ዶክተር ብርሃኑና የፓርቲያቸዉ አመራሮች የትግል ርምጃ
ረቡዕ፣ ሐምሌ 15 2007ማስታወቂያ
ቁጥራቸዉ ይፋ ያልተደረገዉ የአርበኞች ግንቦስ ሰባት የአመራር አባላትን ይዘዉ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወደኤርትራ ያመሩት ሌሎች አማራጮችን ጨምሮ በወታደራዊ ትግልና በሕዝባዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ገዢ ፓርቲ ለማስወገድ መሆኑን የንቅናቄዉ የአመራር አባል ተናግረዋል። ለንደን የሚኖሩት የአርበኞች ግንቦት ሰባት የአመራር አባል ዶክተር ታደሰ ብሩ ለዶይቸ ቬለ እንደገለፁት ዶክተር ብርሃኑ እና ጓዶቻቸዉ ትግሉ ወደሚካሄድባቸዉ አካባቢዎች ያመራሉ። መጀመሪያ ኤርትራ ቢሄዱም ግማሾቹ ታጋዮች ኢትዮጵያ ዉስጥ ስላሉ ወደኢትዮጵያም ገብተዉ ለታጋዮቹ አመራር እየሰጡ እንደሚታገሉ ገልጸዋል። ዝርዝሩን የዋሽንግተኑ ዘጋቢያችን መክብብ ሸዋ ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ