1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዩኤስ አሜሪካ፡ እስራኤል እና የመካከለኛው ምስራቅ የሰላም ሂደት

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 21 2001

ዩኤስ አሜሪካ ሰሞኑን ሁለት ከፍተኛ ባለስልጣናትዋን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ላከች።

https://p.dw.com/p/IymE
ጆርጅ ሚቼል እና ቤንያሚን ኔታንያሁምስል AP

እርግጥ፡ የፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ልዩ የመካከለኛ ምስራቅ ልዑክ ጆርጅ ሚቼል እና የመከላከያ ሚንስትር ሮበርት ጌትስ ወደዚሁ አካባቢ የተጓዙት እክል የገጠመውን የመካከለኛ ምስራቅ የሰላም ሂደት እንደገና ለማነቃቃት ነው። በሳምንቱ አጋማሽም አሜሪካዊው የብሄራዊ ጸጥታ አማካሪ፡ ጂም ጆንስ አካባቢውን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል። ይሁንና፡ እስራኤል በያዘችው ዐረባዊ ግዛት፡ በምስራቅ ኢየሩሳሌም ጭምር መስራት የቀጠለችውን የሰፈራ ግንባታ እንድታቆም አሜሪካዊው ፕሬዚደንት ያቀረቡላትን ጥያቄ ያልተቀበለችበት ርምጃዋ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ፈጥሮዋል። እስራኤል ይህንኑ ተጽዕኖ አሳዳሪ ያሜሪካውያን ልዑካን ጥረት እንዴት ትመለከተዋለች?

ዜናነህ መኮንን/አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ