ዩኤስ አሜሪካ በሶማልያ የአየር ድብደባ አካሄደች
ማክሰኞ፣ ነሐሴ 27 2006ማስታወቂያ
በደቡብ ሶማልያ የታህታይ ሸበሌ ሀገረ ገዥ አብዱካዲር ሞሃመድ ኑር እንደተናገሩት፤ ጥቃቱ በተለይ ያነጣጠረዉ የአሸባብ መሪ በሆኑት አህመድ አብዲ ጎዳኔ እና በሌሎች የቡድኑ መሪዎች ላይ ነበር። የቡድኑ መሪዎች በጥቃቱ መገደል አለመገደላቸዉ በግልፅ የታወቀ ነገር ባይኖርም፤ በአየር ጥቃቱ የሟቾች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል በሶማልያ ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጥ ሕዝብ የከፍተኛ የረሃብ አደጋ ተደቅኖበታል፤ 220 ሽ ከአምስት ዓ,መት በታች የሆኑ ህፃናት በምግብ እጥረት እየተሰቃዩ ነዉ ሲል የመንግሥታቱ ድርጅት ስጋቱን ገልፆአል። ዩኤስ አሜሪካ በሶማልያ በሰው አልባ አይሮፕላን ስላካሄደችውን የአየር ጥቃት ከዋሽንግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገናል።
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ