1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዩኤስ አሜሪካ በሩዋንዳ ላይ የጣለችዉ ማዕቀብ

ዓርብ፣ መስከረም 24 2006

ዩናይትድ ስቴትስ ለሩዋንዳ የምትሰጠዉን ወታደራዊ እርዳታ እንደምታቆም አስታወቀች። የዋሽንግተን አስተዳደር እንዳለው እርዳታው የሚቋረጠው ሩዋንዳ ፣ ህፃናትን በውትድርና በማሰለፍ የሚከሰሰውን

https://p.dw.com/p/19tul
ARCHIV - Kinder-Soldaten der so genannten Union Kongolesischer Patrioten (UPC) patrouillieren durch die Straßen von Bunia in Kongo (Archivfoto vom 19.06.2003). Die Vereinten Nationen gedenken eines der dunkelsten Kapitel in der Geschichte der Menschheit. An diesem Sonntag (25.03.2007) jährt sich das Verbot des transatlantischen Sklavenhandels im UN-Kalender zum 200. Mal. Doch das Thema Menschenhandel ist bis heute nicht bewältigt. Als Beispiele führt UN-Generalsekretär Ban auch das Schicksal von Kindersoldaten an. Foto: Maurizio Gambarini (zu dpa-Korr. "Menschenhandel blüht auch 200 Jahre nach Ende der Sklaverei" vom 22.03.2007) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

በዴሞክራቲክ ኮንጎ የሚንቀሳቀሰዉን M23 የተሰኘዉ ቡድን ትደግፋለች ሲል ባቀረበው ምክንያት ነው ። የሩዋንዳ መንግሥት ግን የዩናይትድ ስቴትስን ክስ አይቀበልም። ዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ትናንት እንዳስታወቀው ሩዋንዳ በተጣለባት ማዕቀብ ምክንያት ዩናይትድ ስቴትስ የምትሰጠው ዓለም ዓቀፍ ወታደራዊ የትምህርትና የሥልጠና እርዳታ ይቋረጥባታል ። የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ ማሪየ ሃርፍ እንደገለጹት የአሜሪካንንወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለመግዛትና አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበትን ወታደራዊ የፋይናንስ ድጋፍም አታገኝም ። መሰል ወታደራዊ ማዕቀብ የሚጣለው በሩዋንዳ ላይ ብቻ ሳይሆን በሱዳን፤ በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እና በማይንማርም ላይ መሆኑን ትናንት አስታወቋል። ሆኖም ሱዳን፣ ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክና ማይንማር እስካሁን ከዩኤስ አሜሪካ ወታደራዊ ድጋፍ ያግኙ አያግኙ ግልፅ ግልጽ አይደለም። በዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሊንዳ ግሪንፊልድ እንዳስታወቁት፤ የመንግሥታቸው ዓላማ ህፃናትን በውትድርና እንዳይሰማሩ ና እንዳይመለምሉ ከሚያደርጉ ሃገራት ጋር በትብብር መስራት ነው። ረዳት ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ላይ ማዕቀብ የተጣለው ሃገሪቱ ህፃናትን በውትድርና የሚመለምለውንና የሚያሰልፈውን M23 የተባለውን ቡድን በመደገፏ መሆኑን አስታውቀዋል። በሩዋንዳ ላይ የተጣለዉ ማዕቀብ ህጻናት በማንኛዉም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ላይ መሳተፋቸዉ እስካልቆመ ድረስ፤ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። ዩኤስ አሜሪካ ሩዋንዳ ቡድኑን ለመደገፏ በማስረጃነት የምታቀርበው ዓለም ዓቀፉ የስብዓዊ መብት ተሟጋች ሂዩመን ራይትስ ዋች ስለ ሩዋንዳ ያወጣውን ዘገባ ነዉ ።ሂዩመን ራይትስ ዋች ዘገባውን ያቀረበው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማነጋገር መረጃዎችን ካሰባሰበ በኋላ ነበር። የሂዩመን ራይትስ ዋች አጥኚ ካሪና ቴርትሳኪን እንደሚሉት ሩዋንዳ አማፂውን M23ን የምትረዳው በተለያየ መንገድ ነው፤

ARCHIV - Ein 10 Jahre alter Kämpfer der so genannten Union Kongolesischer Patrioten (UPC) beim Schusstraining am 14.6.2003 am Rande von Bunia im Kongo in Afrika. Weltweit werden nach Schätzungen von Menschenrechtsorganisationen bis zu 300 000 Kinder in mehr als 20 Ländern als Soldaten missbraucht. Auf Vorschlag Deutschlands beschäftigt sich der UN-Sicherheitsrat am Dienstag (12.07.2011) mit dem Schicksal von Kindersoldaten. Foto: Maurizio Gambarini dpa (zu dpa 0240 vom 12.07.2011) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture alliance/dpa

« ሩዋንዳ የምትሰጠው ድጋፍ የተለያየ ቅርፅ አለው ። ለምሳሌ የታጠቁና የደንብ ልብስ የለበሱ ወታደሮች ከሩዋንዳ ወደ ኮንጎ ድንበር አቋርጠው በተደጋጋሚ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አንዱ ነው ። ኮንጎ ለሚገኘው ለ M 23 የጦር መሣሪያዎችን ጥይቶችንና ምግብ ማቅረብን ያካትታል ። ከM23 ጋር የሚዋጉ ወጣት ወንዶችን ከሩዋንዳ መመልመልንና በመጨረሻም የሩዋንዳ ወታደራዊ መኮንኖች በኮንጎ ድንበር ላይ በተካሄደ የአዳዲስ የ M 23 ምልምሎች ሥልጠና ላይ መሳተፈቸውንም ይጨምራል»

ዩናይትድ ስቴትስ በጉዳዩ ላይ ከሩዋንዳ መንግስት ጋር ዉይይት እንደምትቀጥል በዩኤስ አሜሪካ የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ፀሃፊ ሊንዳ ግሪንፊልድ ገልጸዋል።

M23 rebel soldiers keep guard during the inauguration of newly elected M23 Rebel political wing President, Bertrand Bisimwa in Bunagana on March 7, 2013. The rebel group has parted ways with their former President Bishop Jean-Marie Runiga after allegations of misuse of funds and supporting Bosco Ntaganda, a wanted war criminal. AFP PHOTO/ ISAAC KASAMANI (Photo credit should read ISAAC KASAMANI/AFP/Getty Images)
ምስል Isaac KasamaniAFP/Getty Images

የተመድ እና የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፤ በኮንጎ እና ሩዋንዳ ወሰን ላይ የሚንቀሳቀሰዉ አማጺውን ቡድን M23ን፤ ሰዎችን በመግደል ወንጀል፤ ዉጥረት በበረታበት አካባቢ፤ ሕጻናትን በዉትድራና በማሳማራት፤ እና ህብረተሰቡንም ከቤት ንብረቱ በማፈናቀል ወንጀል፤ በተደጋጋሚ መክሰሳቸዉ ይታወቃል። የቀድሞ የኮንጎ ጦር አባላት ስብስብ የሆነው ቱትሲዎች የሚያመዝኑበት M23 የተባለው አማፂ ቡድን ደግሞ፣ እጎአ በ2009 ዓ,ም የተደረሰበትን የሰላም ስምምነት አላከበረም ሲል የኮንጎ መንግስት ይከሳል።

ሩዋንዳ የM23አማጺያን ትረዳለች በሚል በተደጋጋሚ ብትወነጀልም፤ የኪጋሊ መንግስት ግን ሲያስተባብሉ ቆይቷል ።አሜሪካን በሩዋንዳ ስለጣለችው ማዕቀብ የሩዋንዳ ጦር ዛሬ በሰጠው አስተያየት ሃገሪቱ በማይመለከታት ጉዳይ ተጠያቂ መሆኗ አስገራሚ መሆኑን አስታውቆ ሩዋንዳም ህፃናትን በውትድርና ከሚያሰልፉ ሃገራት ጋር መደመሯ መረጃ አልባ ነዉ ሲል አጣጥሎአል።

አዜብ ታደሰ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ