የ29 ኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመግባቢያ ሰነድ
ዓርብ፣ ጥር 17 2005ከሚያዚያው የአካባቢና የአዲስ አበባ አስተዳደር ምርጫ ራሳቸውን ያገለሉት 29 የፖለቲካ ፓርቲዎች አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሰነድ አዘጋጁ ። ከፓርቲዎቹ የተውጣጣው ጊዜያዊ ኮሚቴ እንዳስታወቀው ረቂቅ ሰነዱ ለፓርቲዎቹ የተበተነ ሲሆን ፓርቲዎቹም ነገ በሚያካሂዱት ስብሰባ በረቂቅ የመግባብያ ሰነዱ ላይ ይመክራሉ ። የሰነዱን ምንነትና አላማ
የ29 ኙ ፓርቲዎች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አሥራት ጣሴ ለዶቼቬለ ተናግረዋል
መጀመሪያ 33 አሁን ደግሞ ቁጥራቸው ወደ 29 ዝቅ ያለው እነዚሁ ፓርቲዎች የተሰባሰቡት በአዳማ ከተማ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀው የምርጫ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በተገኙበት አጋጣሚ ነበር ።
በወቅቱም በጋራ 18 ጥያቄዎችን ለምርጫ ቢቦርድ ቢያስገቡም ጥያቄዎቻቸው ውድቅ ስለሆኑባቸው ራሳቸውን ከሚያዚያው ምርጫ ለማግለል መገደደቻውን አስታውቀዋል ። ከዚያን ወዲህ የጋራ የመግባቢያ ሰነድ እስከማዘጋጀት የደረሱት ፓርቲዎች አሁን በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ አብረው ሲሰሩ ወደፊት ደግሞ ትብብሩን ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር እቅድ እንዳላቸውም አቶ አሥራት ተናግረዋል ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው በሁለት ተከታታይ ምርጫዎች ያልተሳተፈ ፓርቲ እውቅና ይነፈጋል ። አቶ አሥራት ከ29 ኙ ፓርቲዎች በዚህ አሠራር ችግር ላይ የሚወድቅ አለመኖሩን ገልፀዋል ። ሆኖም ይህ ያሰጋል ተብሎ ባላመንበት አካሄድ መሳተፍ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል ።
በምርጫ አብሮ መሥራት ተገቢ መሆኑን ያሳወቁት አቶ አሥራት ሌላውን እየተዉ መሄድ ግን ወደ ፖለቲካ ፍጥጫ የሚያመራና የሚደገፍ አሥራርም እንዳልሆነ ለዶቼቬለ በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል ።
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ