1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፖሮሼንኮ የብራሰል ጉብኝት

ሐሙስ፣ ነሐሴ 21 2007

ሁለቱ ወገኖች ባልፀናው በዩክሬን የተኩስ አቁምና ኬቭ በተጋረጠባት የኤኮኖሚ ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ማካሄዳቸው ተዘግቧል ።የኬቭን መንግሥት የሚደግፈው የአውሮፓ ህብረት ሃገሪቱ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ የተሃድሶ እርምጃዎችን እንድትወስድ ይፈልጋል ።

https://p.dw.com/p/1GN0p
BelgienTreffen Poroschenko und Juncker Brüssel
ምስል Reuters/Y. Herman

[No title]

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፔትሮ ፖሮሼንኮ ዛሬ ብራሰልስ ቤልጂግ ውስጥ ከአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ ። ፕሬዝዳንት ፖሮሼንኮ ፣ከአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ዦን ክሎድ ዩንከር እና ከአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ቱስክ ጋር በተለይ ባልፀናው በዩክሬን የተኩስ አቁምና ኬቭ በተጋረጠባት የኤኮኖሚ ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ማካሄዳቸው ተዘግቧል ።የኬቭን መንግሥት የሚደግፈው የአውሮፓ ህብረት ሃገሪቱ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ የተሃድሶ እርምጃዎችን እንድትወስድ ይፈልጋል ። ስለዛሬው የፖሮሼንኮ የብራስልስ ቆይታ የብራሰልሱን ዘጋቢያችንን ገበያው ንጉሴን ስቱድዮ ከመግባታችን በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።