የፖሮሼንኮ የብራሰል ጉብኝት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 21 2007ማስታወቂያ
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፔትሮ ፖሮሼንኮ ዛሬ ብራሰልስ ቤልጂግ ውስጥ ከአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ ። ፕሬዝዳንት ፖሮሼንኮ ፣ከአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ዦን ክሎድ ዩንከር እና ከአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ቱስክ ጋር በተለይ ባልፀናው በዩክሬን የተኩስ አቁምና ኬቭ በተጋረጠባት የኤኮኖሚ ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ማካሄዳቸው ተዘግቧል ።የኬቭን መንግሥት የሚደግፈው የአውሮፓ ህብረት ሃገሪቱ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ የተሃድሶ እርምጃዎችን እንድትወስድ ይፈልጋል ። ስለዛሬው የፖሮሼንኮ የብራስልስ ቆይታ የብራሰልሱን ዘጋቢያችንን ገበያው ንጉሴን ስቱድዮ ከመግባታችን በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።