የፖላንዱ ረቂቅ ሕግና ተቃውሞው
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 25 2008ማስታወቂያ
ትናንት ከአውሮጳ ሕብረት በኩል የተሰነዘረበት ነቀፌታ እንዳስገረመው ገልጧል። አዲሱ ሕግ ቀደም ሲል የተሾሙ በመንግሥት ቁጥጥር ስር የሚገኙ ሬዲዮኖች እና ቴሌቪዥኖች ሥራ አስኪያጆችን የሥራ ዘመን እንዲያበቃ ያስችላል። ከዚያ በተጨማሪ ሕጉ መንግሥት አዲስ ሥራ አስኪያጆችን መሾም እንዲችል ያደርጋል ተብሎለታል። የፖላንድን አዲሱን የመገናኛ አውታሮች ሕግ በተመለከተ የብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሤን ቃለ-መጠይቅ አድርጌለት ነበር። ሕጉ ከአውሮጳ ሕብረት ለምን ተቃውሞ እንዳስነሳ በማብራራት ይጀምራል።
አዲሱ የፖላንድ የመገናኛ አውታሮች ሕግ በምክር ቤት ከጸደቀ በኋላ 4 የመንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያዎች አስተዳዳሪዎች ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን አሳውቀዋል። አዲሱ ሕግ በፖላንድ ፕሬዚዳንት አንድሪዬ ዱዳ ይፈረማል ተብሎ ይጠበቃል።
ገበያው ንጉሤ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ