የፍርድ ቤት ዉሎ
ዓርብ፣ ግንቦት 30 2005ማስታወቂያ
ላለፉት 15 ቀናት በእስር የቆየዉ ወጣት ብርሃኑ በአምስት ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ነዉ የአዲስ አበባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የወሰነዉ። ወጣቱ መጀመሪያ ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀዉን ሰላማዊ ሰልፍ ታስተባብራለህ የሚል ምርመራ እንደተካሄደበት እና ኋላም ለግንቦት ሰባት ቅስቀሳ ታካሂዳለህ የሚል ምርመራ ይካሄድበት እንደነበር የማኅበሩ ፕሬዝደንት ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። በሌላ የፍርድ ቤት ዜና ደግሞ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች ማኅበር ፕሬዝደንትና ሌሎች ሁለት የአመራር አባላት በማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረዉ ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ በዋስ ተለቀዋል። ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዘገባ ልኮልናል
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ