የፀሐይ ግርጃ በእስያ፣
ረቡዕ፣ ሐምሌ 15 2001ማስታወቂያ
250 ኪሎሜትር ገደማ ስፋት ባለው ቦታ ከህንድ፣ በቻይና በኩል እስከጃፓንና ምዕራባዊው ሰላማዊ ውቅያኖስ የዘለቀው ፀሐይ ሙሉ በሙሉ ለ 6 ደቂቃ ከ 39 ሴኮንድ የተጋረደችበት የተፈጥሮ ትርዒት መታየት የጀመረው፣ በህንድ፣ ጎህ ሲቀድ ፣ ከሌሊቱ ፣ ከ 5 ሰዓት ከ 28 ደቂቃ ጀምሮ(እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ፣ 11 ሰዓት ከ 28 ደቂቃ ላይ)ነው።
ይህን የተፈጥሮ ትርዒት በብዛት ህዝብ ሲያየው ያሁኑ የመጀመሪያ ጊዜ ነው። በዘመናዊ ሥነ-ቴክኒክ በመገሥገሥ ላይ በሚገኙትና ጥንታዊ ባህል ባላቸው በሁለቱ አገሮች ፣ ሳይንስና ባህላዊ አመለካከትም ሆነ እምነት መጋጨታቸውንም ለመታዘብ ተችሏል። በጉጉት፣ ትርዓቱን ለማየት ከመነሣሣት አንስቶ በፍርሃት መዋጥ ፣ ሁኔታውን መጥፎ ገድ አድርጎ የመመልከቱ ሁኔታም የተዛመተ መሆኑ የታወቀ ነው።
ተክሌ የኋላ
አርያም ተክሌ