1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጦር መሳሪያ ርክክብ በሊቢያ

ሰኞ፣ መስከረም 21 2005

ከአንድ ሳምንት በፊት ነበር የሊቢያ አዲሱ መንግስት የቀድሞው የሐገሪቱ የሙአመር ጋዳፊን ገዢ ስርዓት ለማስወገድ ጠመንጃ የታጠቁ በሙሉ መሳሪያቸውን ለፖሊስ እንዲያስረክቡ ማሳሰቢያ ያስተላለፈው።

https://p.dw.com/p/16I9m
epa03415174 A Libyan man hands over his weapon to army officers during a ceremony in Tripoli, Libya, 29 September 2012. Libyans began handing over their weapons as the government launched an initiative in the northern African country to curb arms proliferation. Ordinary people and militiamen, who fought in an armed uprising that deposed the regime of Muammar Gaddafi last year, turned out in high numbers in the capital Tripoli and the eastern city of Benghazi to surrender firearms and ammunition. EPA/SABRI ELMHEDWI
ምስል picture-alliance/dpa

የአዲሱን መንግስት ትዕዛዝ በመከተል እስካሁን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሊቢያውያን ትጥቃቸውን ፈተዋል። ይሁንና በሺዎች የሚቆጠሩ ወሳሪያዎች እስካሁን በመንግስት እጅ አልገቡም። አንድ ወጣት ሊቢያዊ በጁ ሙሉ የያዛቸውን ጥይቶች ጠረቤዛ ላይ ይዘረግፋል። የአዲሱ የሊቢያ ፖሊስ ደግሞ ካላሺንኮፍ ውስጥ የሚገቡትን ጥይቶች ቆጥሮ ይረከባል። 21 ናቸው። ይህም በመዝገብ ይያዛል። ሌላ ጠረጴዛ ላይ ደግሞ እንዲሁ ሌላ ሰው ሽጉጡን ያስረክባል። ትጥቅ ፈቺው ወደ ፖሊስ ጣቢያ የመጣበትን ምክንያት እንደሚከተለው ይገልፀዋል።

« የዚህ ርምጃ አካል መሆን ስለፈለኩ ነው ሽጉጤን የመለስኩት። አገራችን የተረጋጋች እና ሰላም የሰፈነባት እንድትሆን እፈልጋለሁ። መሳሪያ የትም ተበትኖ እንዲቆይ አንፈልግም። የምንፈልገው ነገር ቢኖር ሰላም የሰፈነበት ህይወት ነው። የአምባገነኑን ስርዓት ተገላግለናል፤ ስለዚህ ጠመንጃ አያስፈልገንም።»

ይሁንና 200 000 የሚደርሱ የጦር መሳሪያዎች አሁንም በሀገሪቱ ተበትነው እንደሚገኙ ይገመታል። ፈንጂዎች፣ ሽጉጦች እና ጥይቶቹ የተገኙት ከቀድሞው ገዢ ሙአመር አል ጋዳፊ የጠመንጃ ስብስብ ነው።

ከ800 በላይ ሽጉጦች፣ 200 ጓዳ ሰራሽ ፈንጂዎች፣ 100 የታንክ ጥይቶች እና 20 000 የጠመንጃ ጥይቶች 6 ሮኬቶች እና አንድ ታንክ ለማስረከብ በተቋቋሙ ጣቢያዎች ተመላሽ ሆነዋል።

A Libyan man hands over his weapon to Libyan Army Chief of Staff Yussef al-Mangoush in Tripoli's Martyrs Square September 29, 2012. Hundreds of Libyans handed over weapons to the military in Tripoli and the eastern city of Benghazi as the authorities try to clean the streets from arms left over from last year's war. REUTERS/Ismail Zitouny (LIBYA - Tags: POLITICS MILITARY)
የጦር መሳሪያ ርክክብ በትሪፖሊምስል Reuters

ይህ ገና መጀመሪያው ነው። በዚህ አይነት መንገድ ብቻ ነው የሊቢያ ደህንነት ሊሻሻል የሚችለው ይላል ሌላ ሽጉጡን ሊመልስ የመጣው ሊቢያዊ፤« ቀን በቀን ሲካሄድ የነበረው መታኮስ በቅቶናል ነው ያለው አንዱ ታጣቂ፤ አዎ ይህ ይበቃል። መቆም አለበት ሁሉም ጥይቁን ማስረከብ አለበት።»

ከተረካቢዎቹ አንዱ ፖሊስ ይህንን የትጥቅ መፍታት ሂደት በአድናቆት ሲመለከት ቆይቷል። ድርጊቱም በዚህ መልኩ ለሚቀጥሉት ሳምንታት መቀጠል አለበት ባይ ነው።

ባለፉት ሁለት ሳምንታት አነጋጋሪ በነበረው እስልምናን የሚያንቋሽሽ ፊልም ሳቢያ በተነሳው ተቃውሞ ቤንጋዚ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ ለደረሰው ጥቃት ፣ ለአምባሳደሩ እና ለሌሎች ሶስት ባለስልጣናት ሞት መነሻ የሆነው በአመፁ ላይ ተሳታፊዎች መሳሪያ እንደ ልብ ስለታጠቁ ነው የሚሉ አልጠፉም። ይሁንና የዮናይትድ ስቴትስ የስለላ ቡድን በሳምንቱ መጨረሻ እንዳስታወቀው፤ መስከረም 1 ቀን በአሜሪካ ኤምባሲ ላይ የደረሰው ጥቃት ሆን ብሎ በአልቃይዳ የታቀደ ነው።

ያም ሆነ ይህ ግን በሊቢያ መረጋጋት እንዲሰፍን ህዝቧ ጦር መፍታት አለበት።የዶይቸ ቬለ ዘጋቢ ፔተር በቦታው በመገኘት እንደተከታተለው ከሆነ በጥብቅ ቁጥጥር መበመካሄድ ላይ የሚገኘው የጦር መሳሪያ ምለሳ አሰራር ሽልማት ስለሚያስገኝ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በህዝቡ ዘንድ ድጋፍ ያገኘ ይመስላል። ጠመንጃ እና ጥይት ላስረከቡት እጣ ይወጣና፤ በስተመጨረሻ ሁለት ሰዎች የመኪና ባለቤት ይሆናሉ።

ፔተር እሽቴቬ

ልደት አበበ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ