1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የጤና ሁኔታ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 12 2004

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የጤና ሁኔታ የሃገሪቱን ህዝብ ማነጋገሩን ቀጥሏል ። አቶ መለስ በጠና መታመማቸውና ብራሰልስ ቤልጅየም መታከማቸው ከተለያዩ ምንጮች ተሰምቷል ። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን ዜና በማስተባበል ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ

https://p.dw.com/p/15b7I
ምስል AP

 በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ማስታወቁን የሃገር ውስጥና የውጭ የዚና ወኪሎች ዘግበዋል ። ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የጤና ሁኔታ ለማጣራት ዶቼቬለ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትንም ሆነ የቤልጂግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ሃላፊዎችን ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም ። ሂሩት መለሰ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ መታመማቸውና ህክምና ላይ የመሆናቸው ጭምጭምታ መሰማት ከጀመረ ጥቂት ወራት ተቆጥረዋል ። የጤናቸው ሁኔታ አነጋጋሪነት ተጠናክሮ የቀጠለው ግን መለስ ሰኔ መጨረሻ ላይ በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስበሰባ ላይ ሳያገኙና በኃላም ባለፈው ሳምንት እሁድና ሠኞ በተካሄደው የአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሳይካፈሉ ከቀሩ በኋላ ነው ። ባላፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ደገሞ ብራስልስ ቤልጅየም ውስጥ በሚገኝ ሉክ በተባለ ሆስፒታል ታከሙ የተባሉት አቶ መለስ ሳያርፉ አልቀረም የሚሉ መላምቶችም መሰንዘር ጀምረው ነበር ። እነዚህን የመሳሰሉ የተለያዩ አስተያየቶች ከተለያዩ ምንጮች ሲሰሙ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የጤና ሁኔታ ምንም ነገር ሳይባል መታመማቸው በአፍሪቃ ህብረት ጉባኤ ወቅት ነበር በይፋ የተነገረው። በአዲሱ የአፍሪቃ የልማት አጋርነት ወይም ኔፓድ ስበሰባ መክፈቻ ላይ የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማክ ሳሊ መለስ በጤና እክል ምክንያት አለመገኘታቸውን ካሳወቁ በኋላ

Bei der Einweihung der Konstruktion für den neuen Hafen auf Lamu: Kenias Premierminister Raila Odinga, Präsident Südsudan, Salva Kiir, Präsident Kenias, Mwai Kibaki, Äthiopischer Premierminister, Meles Zenawi und Kenias Vizepräsident, Kalonzo Musyoka (v.l.n.r.) (2.3.2012) Copyright: DW/ Eric Ponda
መለስ በኬንያው የላሙ ወደብምስል DW

የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ብሉምበርግ ለተባለው የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ቃለ ምልልስ አቶ መለስ ከባድ ሳይሆን ቀላል ህመም እንዳጋጠማቸው ፣ እንደማንኛውም ስው ህክምና እንደሚያስፈልጋቸውና በቅርቡም እንደሚመለሱ ተናግረዋል ። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ኤ.ኤፍ.ፒ ትንንት ባሰራጨው ዜና ግን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በጠና ታመው ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምና እንድተደረገላቸው አንዳንድ ዲፕሎማቶች መናገራቸውን አስታውቋል ። በዚሁ ዘገባ የ 57 ዓመቱ የአቶ መለስ የጤና ሁኔታ አስጊ መሆኑ ተጠቁሟል ። ሆኖም የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ በረከት ስምኦን፦ አቶ መለስ «በጠና አልታመሙም፤ ጤናቸውም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል» ማለታቸዉን ኤ,ኤፍ,ፒ በዘገባው ጠቅሷል ።

አቶ መለስ ብራሰልስ ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው ስለመሆን አለመሆኑ በብራሰልስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ እንዲሰጠን ከዶቼቬለ የአማርኛዉ ክፍል ከትናንት በስተያ ላቀረብነዉ ጥያቄ፦-ኤምባሲዉ በኢሜይል በላከልን መልስ፤ አቶ መለስ በህክምና ላይ ናቸው መባሉን «ሃሰትና ስህተት» በማለት ገልፆ ታመሙ የሚለዉን ዜና «የሃሰት ታሪኮችን በማሰራጨት በተጠመዱና በተወሰኑ ወገኖች የተፈጠረ » በማለት አጣጥሎታል ።ኤምባሲው ይህን ቢልም የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ግን አቶ መለስ ለተወሰኑ ቀናት ብራሰልስ ከሚገኙት ዋና ዋና ሆስፒታሎች በአንዱ በግል መደበኛ ህክምና እንደተደረገላቸው ብራሰልስ የሚገኙ አንዳንድ ዲፕሎማቶች መናገራቸውን አስታውቋል ።

epa03026163 Meles Zenawi, Prime Minister of Ethiopia speaks during the opening plenary session of the High Level Segment of the COP 17 / CMP 7 United Nations (UN) Climate Change Conference 2011 in Durban, South Africa, 06 December 2011. The 17th session of the Congress of the Parties (COP) comprising 194 countries meeting to discuss the United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC) began its High Level Segment serving as the meeting of the Parties to the Kyoto Protocol. EPA/NIC BOTHMA
ምስል picture-alliance/dpa

ዶቼቬለ ስለ መለስ የጤና ሁኔታ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት መረጃ ለማግኘት ከዚህ ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም ። አቶ መለስ ብራሰልስ መታከም አለመታከማቸውን እንዲያረጋግጥ ዶቼቬለ ለቤልጂግ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጥያቄ ቢያቀርብም የመስሪያ ቤቱ ምክትል ቃል አቃባይ በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት መግለጫ ሆነ ማስተባበያም እንደማይሰጡን ነው በስልክ የነገሩን ። ሆኖም ሪፖርተር ጋዜጣ ጠቅላይሚኒስትሩበመጪዎቹጥቂትቀናትውስጥየውጭሕክምናክትትላቸውንጨርሰውወደኢትዮጵያእንደሚመለሱየምንጮቹን ማንነት ሳይገልፅ ዘግቧል ። በዚሁ ዘገባ እንደተጠቆመውመለስ፣ወደአገራቸውሲመለሱወዲያውኑ ሥራ እንደማይጀምሩና ለተወሰኑጊዜያትካለባቸውከባድኃላፊነትርቀውዕረፍትእንዲያደርጉበሐኪሞቻቸውመመከራቸውንማንነታቸውን ካልጠቀሳቸው ምንጮችመስማቱን ሪፖርተር አስታውቋል ። የሕመማቸውምምክንያትምየሥራጫናመሆኑ ነው የተመለከተው ።ይህን መረጃ ግን ከመንግሥት ባለሥልጣናት ማረጋገጥ አልቻልንም ።

ጠቅላይሚኒስትሩሕክምናቸውንሲከታተሉበትየቆዩበትአገርለደኅንነታቸውሲባልእንዳይገለጽጠይቀዋል ያላቸውምንጮቹ ፣ከፍተኛየመንግሥትባለሥልጣናትመለስን ያሉበት ድረስ ሄደው እንደጎበኙዋቸውም ዘግቧል  ። ላለፉት 21 ዓመታት ኢትዮጵያን በፕሬዝዳትነት እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት አቶ መለስ ዜናዊ 20 ዓመት ሳይሞላቸው ነበር የህክምና ትምህርታቸውን አቋርጠው የደርግ መንግሥትን ለመውጋት የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር ህወሀትን የተቀላቀሉት ።በ1981 ዓም የግንባሩን መሪነት የተረከቡት መለስ  ከዓመታት በኋላ ግንባሩ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ተዋህዶ የመሰረተው ፣ የአሁኑ ገዥ ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ኢህአዲግ ሊቀመንበርም ናቸው ።  በተቃዋሚዎችና በሰበዓዊ መብት ተሟጋቾች ሰብዓዊ መብትን በመጣስ የፕሬስ ነፃነትን በመጨቆንና ተቃዋሚዎችን በማዋከብ የሚወገዙት መለስ በደጋፊዎቻቸው ደግሞ ባለራዕይ መሪ ተደረገው ይወደሳሉ ። ለጊዜው የመለስ ህመም ምንነትም ሆነ ለምን ያህል ጊዜ ከህዝብ እይታ ተሰውረው እንደሚቆዩ ግልፅ አይደለም ። በአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ እርሳቸውን ተክተው የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ናቸው ። አቶ ኃይለ ማርያም እስከ መቼ የእሳቸውን ቦታ ሸፍነው እንደሚሰሩም በግልፅ የታወቀ ነገር የለም ።

Kenya's President Mwai Kibaki and Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi (L) applaud after the signing of bilateral agreements between the two countries at the State House in Nairobi, March 1, 2012. The leaders expressed confidence that the Lamu Port-South Sudan-Ethiopia (LAPSSET) project will unlock trade and investment opportunities between the two countries once realized. REUTERS/Thomas Mukoya (KENYA - Tags: POLITICS BUSINESS)
መለስ ዜናዊ ከምዋይ ኪባኪ ጋርምስል Reuters