የጎምቱው ፖለቲከኛ ኃይሉ ሻውል መታሰቢያ
ሰኞ፣ ጥቅምት 7 2009ማስታወቂያ
በ1997 ዓ.ም የድኽረ ምርጫ ኩኸት ለእስር ከተዳረጉት እና ኋላ በወቅቱ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ከተፈቱ ፖለቲከኞች እና ምሁራን መካከል አንዱ ኃይሉ ሻውል ነበሩ። በ80 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ጎምቱ ፖለቲከኛ በአባይ ሸለቆ ጥናት በማድረግ ይታወቃሉ። ኃይሉ ሻውል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ኃላፊም ነበሩ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እንዲሁም የቅንጅት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ፕሬዝዳንት በመሆን ላገለገሉት ኢንጂኔር ኃይሉ ሻውል በተዘጋጀ የመታሰቢያ መሰናዶ ላይ የተገኘው የአዲስ አበባው የዶይቼ ቬለ ወኪል ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ የሚከተለውን ዘገባ አድርሶናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
እሸቴ በቀለ
ሒሩት መለሰ