የግንቦት 20 25ኛ ዓመት አከባበር
ቅዳሜ፣ ግንቦት 20 2008ማስታወቂያ
በዓሉ ዛሬ ሲከበር፤ ዜጎች ከቁም እስር አልተላቀቁም፣ ጥቂቶች እየከበሩ ብዙኃኑ የበይ ተመልካች ሆኗል የሚሉ ቅሬታዎችና ቁጭቶች ይደመጣሉ። በሌላ ወገን ሀገሪቱ አድጋለች፤ ከቀድሞ ጭቆናም ተላቀን በዲሞክራሲ እየኖርን ነው የሚሉ ወገኖች በኩራት ሲናገሩ ይደመጣል። ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለረሐብ በተጋለጡባት ኢትዮጵያ ለሚከበረው ለዛሬው የበዓል ስነሥርዓት በተለይ የመንግሥት ሠራተኞች በግድም በውድም እንዲታደሙ የሚያስጠነቅቅ ማስታወቂያ ቀደም ብሎ መለጠፉ ብዙዎችን አነጋግሯል። ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም እና በሚሊኒየም አዳራሽ በመገኘት የበዓሉ አከባበር ምን እንደሚመስል የአዲስ አበባው ወኪላችን
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ