የግብፅ ኮፕቶች 118ኛዉ የሃይማኖት አባት
ሰኞ፣ ጥቅምት 26 2005ማስታወቂያ
ቤተክርስቲያን በምትከተለዉ በእጩነት ከቀረቡ ሶስት አባቶችን አንዱን በእጣ የመለየት ስልት ነዉ። ስነስርዓቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን የወከሉ አባቶችን ጨምሮ በአካል ከሁለት ሺህ በላይ ታዛቢዎች ተከታትለዋል። ምርጫዉ እንዳይጭበረበርና የሰዎች ጣልቃ ገብነት እንዳይኖርበት በጥንቃቄ መከናወኑን የፈረንሳይ የዜና ወኪል ከካይሮ ዘግቧል። ከህዝቡ 10 በመቶ መሆናቸዉ የሚገለፀዉ የግብፅ ኮፕት ክርስቲያኖች ለአክራሪ ሙስሊሞች ተፅዕኖና ጥቃት መጋለጣቸዉን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ከዚህ አንፃር የተመረጡት አባት ምን ይጠብቃቸዋል፤ ሂደቱን ከቅርብ ርቀት የተከታተለዉን የጂዳዉ ወኪላችንን ስለሁኔታዉ በስልክ ስቱዲዮ ከመግባቴ አስቀድሜ አነጋግሬዋለሁ፤
ነብዩ ሲራክ
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ