1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን እና አሜሪካ የስለላ ዉዝግብ

ሰኞ፣ ሰኔ 30 2006

ጀርመን አንድ ዜጋዋ በሀገሪቱ የስለላ ተቋም ተቀጥሮ ለዩናይትድ ስቴትስ እንደሚሰልል ከደረሰችበት ወዲህ ጉዳዩ የሀገሪቱን ከፍተኛ የፖለቲካ ኃይሎች እያነጋገረ ነዉ። በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለመሰላለልን ስምምነት ለመፈረም ዝግጁ አለመሆኗን ዋሽንግተን ባለፈዉ ሳምንት መገባደጃ ላይ አመልክታለች።

https://p.dw.com/p/1CXI7
Symbolbild NSA Spähaffäre
ምስል Reuters

የአሜሪካን የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ቤን ሮደስ ለዘጋቢዎች በጉዳዩ ላይ ባደረጉት ገለፃ ሀገራቸዉ ከየትኛዉም ሀገር ጋ እንዲህ ዓይነት ዉል የላትም ነዉ ያሉት። እንዲህ ያለ አለመግባባትን የሚያስከትል ሁኔታ ሲከሰትም በመነጋገር መፍትሄ እስኪያገኝ ጊዜ እንደሚወስድም ከማመልከት ሌላ መረጃ እንዳቀበለ ስለተደረሰበት ጀርመናዊ ጉዳይ የተባለ ነገር የለም። ግለሰቡ 218 ዶሴዎችን ለዩናይትድ ስቴትስ በ25 ሺ ዩሮ መሸጡን ማመኑ የተገለጸ ሲሆን ቀጣይ ምርመራዎችም እንደሚኖሩ ነዉ የጀርመን የሀገር ዉስጥ ሚኒስትር ቶማስ ዴሜዚር የገለፁት። መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል የተባለዉ እዉነት ከሆነ ከባድ ጉዳይ ነዉ ማለታቸዉ ተዘግቧል። ይህን አስመልክቶ የጀርመን መገናኛ ብዙሃን የሚሉትን አካቶ እንዲያስረዳን የበርሊኑን ዘጋቢያችን ይልማ ኃይለሚካኤልን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ