የጀርመን እና አሜሪካ የስለላ ዉዝግብ
ሰኞ፣ ሰኔ 30 2006ማስታወቂያ
የአሜሪካን የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ቤን ሮደስ ለዘጋቢዎች በጉዳዩ ላይ ባደረጉት ገለፃ ሀገራቸዉ ከየትኛዉም ሀገር ጋ እንዲህ ዓይነት ዉል የላትም ነዉ ያሉት። እንዲህ ያለ አለመግባባትን የሚያስከትል ሁኔታ ሲከሰትም በመነጋገር መፍትሄ እስኪያገኝ ጊዜ እንደሚወስድም ከማመልከት ሌላ መረጃ እንዳቀበለ ስለተደረሰበት ጀርመናዊ ጉዳይ የተባለ ነገር የለም። ግለሰቡ 218 ዶሴዎችን ለዩናይትድ ስቴትስ በ25 ሺ ዩሮ መሸጡን ማመኑ የተገለጸ ሲሆን ቀጣይ ምርመራዎችም እንደሚኖሩ ነዉ የጀርመን የሀገር ዉስጥ ሚኒስትር ቶማስ ዴሜዚር የገለፁት። መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል የተባለዉ እዉነት ከሆነ ከባድ ጉዳይ ነዉ ማለታቸዉ ተዘግቧል። ይህን አስመልክቶ የጀርመን መገናኛ ብዙሃን የሚሉትን አካቶ እንዲያስረዳን የበርሊኑን ዘጋቢያችን ይልማ ኃይለሚካኤልን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ