የጀርመን ና የአየርላንድ ድርጅቶች ርዳታ
ረቡዕ፣ ሰኔ 3 2007ማስታወቂያ
የጀርመን የልማት ተራድኦ ድርጅት በምህፃሩ GIZ ና የአየርላንድ የእርዳታ ድርጅት በደቡብ ክልል በስልጤ ወረዳ ለሚገኘው የዲበባ የጤና ጣቢያ በፀሐይ ሃይል የሚሰራ የህክምና መገልገያ ትናንት አስረከቡ ።ሁለቱ ድርጅቶች የለገሱዋቸው መሣሪያዎች በአካባቢው ለሚኖሩ 29 ሺህ ሰዎች አገልግሎት እንደሚሰጥባቸው ለጋሾቹ ተናግረዋል ። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እርዳታው የኤሌክትሪክ ኃይል ችግር ላለባቸው ጤና ጣባያዎች ጠቃሚ መሆኑን አስታውቋል ። በርክክቡ ስነ ስርዓት ላይ የተገኘው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሀመድ