የጀርመን መራሂተ መንግስት የዩኤስ አሜሪካ ይፋ ጉብኝት
ማክሰኞ፣ ግንቦት 30 2003ማስታወቂያ
አምስት ሚንስትሮች ይዘው ትናንት ወደ ዩኤስ አሜሪካ የተጓዙት ሜርክልከፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ጋ በአፍጋኒስታን እና በሊቢያ እንዲሁም በበርካታ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ዛሬ ማታ በዋይት ሀውስ ቤተመንግስት ለመራሂተ መንግስት ሜርክል ክብር በሚደረገው ይፋ የራት ግብዣ ላይ ፕሬዚደንት ኦባማ ለጀርመናዊትዋ መራሂተ መንግስት በዩኤስ አሜሪካ ለአንድ ሲቭል የሚሰጠውን ከፍተኛ የነጻነት ሜዳልያ ይሸልማሉ።
አበበ ፈለቀ
አርያም ተክሌ