1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የድሬዳዋው የግል ተወዳዳሪ የምርጫ ምልክት

ሐሙስ፣ መጋቢት 17 2007

ከዱር ዐራዊት እስከ ቤት እንስሳት ፤ የመወዳደሪያ ምልክታቸው ለማድረግ ሲመርጡ ፤ ድርጊታቸው አስገራሚም አሥቂኝም ይምሰል እንጂ ፣ ምረጡኝ ባዩ ፣ ቁም ነገር አዘል መፈክርም ሆነ ጉዳይ ሳይሆን አልቀረም አንግበው የተነሱት ።

https://p.dw.com/p/1EyAm
Büro des National Electoral Board of Ethiopia NEBE
ምስል DW

አቶ ሙስጠፋ የተባሉት በድሬዳዋ የሚኖሩ የግል ተወዳዳሪ፣ «ሙስጠፋ ሌቦችን ከገጸ ምድር የሚያጠፋ!» የሚል የምረጡኝ ቅስቀሳም በማካሄድ ላይ ናቸው። የሚጀመረው ካካባቢ ነው ካላሉ በስተቀር ፤ እንዴት ኣድርጎ ነው በዓለም ዙሪያ ያለውን ሌባ ሁሉ ማጥፋት የሚቻለው!? ለማንኛውም ከሰሞኑ በድሬዳዋና በሐረር የምርጫ ዝግጅትን ለመታዘብ ጎራ ብሎ የነበረው ዘጋቢአችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር አነጋጋሮአቸዋል ።

ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር

ተክሌ የኋላ

ሸዋዬ ለገሠ