የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በኢትዮጵያ
ሰኞ፣ መጋቢት 8 2006ለወራት በዘለቀው የደቡብ ሱዳን የርስ በርስ ጦርነት የተነሳ በርካታ ደቡብ ሱዳናውያን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል። ከነዚህ መሸሻ ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ ስትሆን «ዩ ኤን ኤች ሲ አር» በአሁኑ ሰዓት በድንበሩ አካባቢ የሚገኙ ወደ 16 000 የሚጠጉ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን ወደ ሌላ ቦታ የማስፈር ስራ በማካሄድ ላይ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው የ«ዩ ኤን ኤች ሲ አር» የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ክሱት ገብረ እግዚአብሔርን ለጊዜው የወከሉት ወ/ት ቤተል ጌታቸው ስደተኞቹን ወደ ሌላ ቦታ የማስፈሩ ሂደት ምን እንደሚመስል ገልፀውልናል።
ባለፈው ታህሳስ ወር በተቀሰቀሰው ግጭት የታወከችው ደቡብ ሱዳን እስካሁን አልተረጋጋችም። ስደተኞቹ በኢትዮጵያ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆዩ በግልፅ ለመናገር ቢከብድም፤ እንደ ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ግምት ቶሎ አይሆንም። ወደሀገራቸው እስኪመለሱ ድረስ «ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ከለላ ባገኙበት ቦታ ርዳታ ያቀርባል። ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን ከ140 ሺ የሚበልጡ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ከለላ እንዳገኙ ድርጅቱ አክሎ አስረድቶዋል።
በ«ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ዘገባ መሰረት በየቀኑ በአማካይ 20 የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ድንበር ተሻግረው ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ። በአምስት አቅጣጫዎች የሚገኘቱን ድንበሮቿን ለስደተኞች ክፍት ባደረገችው ኢትዮጵያ ውስጥ እስከ ጎርጎሮሲያኑ የካቲት 2014 መጨረሻ ብቻ በጠቅላላ ከ13 ሀገራት የሄዱ ከ 500 143 የሚበልጡ ስደተኞች መመዝገባቸውን ወ/ት ቤተል አስረድተዋል።
እነዚሁ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ከየት ወዴት ነው የሚሰፍሩት? በምን ሁኔታስ ላይ ይገኛሉ? ለሁሉም መልስ ከድምፅ ዘገባው ያገኛሉ።
ልደት አበበ
አርያም ተክሌ