1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደራሲው ግጥም እና የእሥራኤል ርምጃ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 1 2004

በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሰላም ተሸላሚ የሆኑት ዕውቁ ጀርመናዊው ደራሲ ጉንተር ግራስ በኢራን በአወዛጋቢው የአቶም መርሀግብርዋ ሰበብ ከእሥራኤል ጋ የተፈጠረውን ውዝግብ መንሥዔ በማድረግ ባለፈው ሣምንት ሰፊ ተነባቢነት ባለው የሀገራቸው ዕለታዊ ዙድዶይቸ ጋዜጣ «መነገር ያለበት»

https://p.dw.com/p/14Zww
Berlin/ ARCHIV: Der Schriftsteller und Nobelpreistraeger fuer Literatur, Guenter Grass, sitzt in Berlin waehrend der Veranstaltung "Mehr Demokratie wagen! Guenter Grass im Gespraech mit Sigmar Gabriel" anlaesslich der Vorstellung des Buches "Guenter Grass auf Tour fuer Willy Brandt - Die legendaere Wahlkampfreise 1969" im Willy-Brandt-Haus (Foto vom 07.10.11). Auf den Literaturnobelpreistraeger Guenter Grass hagelt es weiter Kritik wegen seines umstrittenen Israel-Gedicht. Der Schriftsteller Rolf Hochhut warf ihm Heuchelei vor. Grass selbst zeigte sich enttaeuscht ueber Antisemitismus-Vorwuerfe und raeumte ein, er haette seine Kritik direkt an die israelische Regierung richten sollen. Foto: Clemens Bilan/dapd
ምስል dapd

በሚል ርዕስ ሥር ያወጡት ግጥም እዚህ ጀርመን እና እሥራኤል ውስጥ አሁንም ማከራከር ይዞዋል። ግራስ በግጥማቸው እንዳስቀመጡት፡ ኢራን የአቶም ጦር መሣሪያ ባለቤት ለመሆን የምታደርገው ጥረት ለሀገርዋ አደገኛ ነው በሚል እሥራኤል በዚችው ሀገር አንጻር ቀድማ የመከላከል የአቶም ጥቃት ልትሰነዝር የምትችልበት ርምጃ የኢራንን ሕዝብ ሊያጠፋ የሚችል ሥጋት ደቅኖዋል። የጀርመን መንግሥትም እሥራኤል ኅልውናዋን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረትዋ ላይ ከጎንዋ መቆሙን ያስታወቀበትንም ድርጊት ግራስ አክለው ነቅፈዋል። ግራስ የአቶም ኃያል መንግሥት ያልዋት እሥራኤል የዓለምን ሰላም ሥጋት ላይ መጣልዋን ነው በግጥማቸው የገለጹት። በዚህም የተነሳ የእሥራኤል ሀገር ውስጥ ሚንስቴር ግራስ ወደሀገርዋ እንዳይገቡ ዕገዳ ጥሎባቸዋል። የእሥራኤል መንግሥት ይህንን ብዙ ታዛቢዎች ጠንካራ ያሉትን ርምጃ ለወሰደበት ምክንያት የሰጠውን ምክንያት እንዲያብራራልን ቀደም ሲል የሀይፋ ወኪላችንን ግርማው አሻግሬን በስልክ ጠይቄዋለሁ።

ግርማው አሻግሬ

አርያም ተክሌ

ተክሌ የኋላ