1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደራሲዉ የብዕር ትግል

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 3 2005

«አፍሪቃ ህዝብ ነዉ። አፍሪቃ ማለት በችግር ዉስጥ ያለ ብቻ ማለት አይደለም። ይህንን ካልተረዳን ደግሞ የሚደረገዉ ርዳታ ተገቢዉን ስኬት ሊያመጣ አይችልም ሰብዓዊነትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል አለብን። »

https://p.dw.com/p/18EFI

ታዋቂዉ ናይጀርያዊዉ ደራሲና የፖለቲካ ሃያሲ ቺኑአ አቼቤ በጎ,አ 2002 ዓ,ም ጀርመንን በጎበኘበት ወቅት አዉሮጳዉያን ስለአፍሪቃ የሚያስቡትና የሰሙትን ስር የሰደደ ትክክለኛ ያልሆነን አመለካከት እንዲቀየሩ ባደረገዉ ንግግር እንዲህ ሲል አሳስቦ ነበር።

ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ በስነ-ጽሑፍ ስራዉ በዓለም አድናቆትን ያገኘዉ ናይጀሪያዊ ደራሲ ፕሮፊሰር ቺኑአ አቼቤ በ82 ዓመቱ ባለፈዉ ሰምወን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይትዋል። ደራሲዉ በስነ ጽሁፍ ስራዎቹ ብቻ ሳይሆን የሚታወቀዉ በጋዜጠኝነት አስተማሪነት እና በጠንካራ ሃያሲነቱም ነበር። የናጀርያዊዉ ደራሲ ቺኑአ አቼቤ የስነ-ጽሁፍ ስራዎች በዓለም አገራት ቋንቋዎች ተተርጉመዉ በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ለስነ-ጽሁፍ ማስተማርያነትም ጥቅም ላይ ዉለዋል። በዕለቱ ዝግጅታችን የፕሮፊሰር ቺኑአ አቼቤን ስራዎች እናያለን የሀገራችንን የስነ-ጽሁፍ ይዘት የሚነግሩንን ምሁራን ጋብዘናል

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ