1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩኤስ አሜሪካ ምርጫ ውጤት እና አንደምታው

ረቡዕ፣ ጥቅምት 26 2007

በዩኤስ አሜሪካ ትናንት በተካሄደው አጋማሽ የምክር ቤት ምርጫ ሬፓብሊካውያን በሁለቱም የምክር ቤት ክፍሎች አሸነፉ። በሕግ መምሪያው ምክር ቤት አብላጫውን ድምፅ የያዙት ሬፓብሊካውያን 100 መንበሮች ባሉት በሕግ መወሰኛው ምክር ቤትም ውስጥ 52 መንበሮችን በማግኘት አብላጫውን ድምፅ መያዝ ችለዋል።

https://p.dw.com/p/1DhDA
Infografik Seats in the 114th United States Congress englisch

የሬፓብሊካኖቹ ፓርቲ በምርጫዉ የተሳካ ውጤት ማግኘቱ የዴሞክራቱ ፓርቲያቸው የተሸነፈባቸው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በቀሩቸው ሁለት የሥልጣን ዓመታት በሚያንቀሳቅሱዋቸው ፖሊሲዎች እና በሚያነሱዋቸው አጀንዳዎች ላይ ወይም በፀደቁ ሕግጋት ላይ፣ ለምሳሌ፣ የጤና መዋቅራቸውን በመሰለው ሕግ ላይ የሚያሳርፈው ተፅዕኖ ይኖር ይሆን? ምንም እንኳን ሬፓብሊካኖቹ ባለፉት ዓመታትም ቢሆን ተባብረው ሲሰሩ ሳይሆን ሲያከላክሉ ቢታዩም። ስለ አሜሪካ ምርጫ አንደምታ የዋሽንግተኑን ወኪላችን አነጋግሬዋለሁ።

Kongresswahlen in den USA (Jubelnde Republikaner)
ምስል Getty Images/M. Piscotty

አበበ ፈለቀ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ