የዩሮ ቀውስና የአውሮፓ መሪዎች ጉባኤ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 14 2004ማስታወቂያ
የዩሮ ተጠቃሚ ሃገራት በገጠማቸው ከባድ ፈተና ላይ መሪዎቹ ባላፈው እሁድ የጀመሩት ውይይት ነገም ይቀጥላል ። በግሪክ ጀምሮ ወደ ሌሌችም የዩሮ ተጠቃሚ አገራት ቀስ በቀስ ለተዛመተው የዕዳ ቀውስ እንዲሁም የጋራውን መገበያያ ገንዘብ ዩሮን ለማረጋጋት በቀረቡት የመፍትሄ ሃሳቦች ላይ በአውሮፓ ህብረት በየደረጃው ምክክር ሲደረግ ና የመፍትሄ ሃሳቦችም ሲቀርቡ ብዙ ወራት አልፈዋል ። ባለፈው እሁድ የተካሄደው የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት የመሪዎች ጉባኤ ከነዚህ ሁሉ የላቀውና ከፍተኛ ትኩረትም የተሰጠው አብይ ጉባኤ ነበር ። በእሁዱ ጉባኤ ላይ የግሪክ የዕዳ ቅነሳ ፣ የአውሮፓ ባንኮችን ከክስረት ለማዳን የቀረበው እቅድ እንዲሁም ለአውሮፓ የገንዘብ ማረጋጊያ ስርዓት መርሃ ግብር የሚመደበው የመጠባበቂያ ገንዘብ መጠን ሙሉ በሙሉ ስምምነት ላይ ሳይደረስባቸው ለነገ የተገፉ ሶሶቱ አብይ ጉዳዮች ናቸው ። መሪዎቹ በነዚህ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ነገ ረቡዕ እንደገና በመምከር ውሳኔ ላይ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ