1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የየመን የለጋሾች ጉባኤ 

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 19 2009

በአሁኑ ጊዜ በየመን በረሀብ ለተጎዱት ከሚያስፈልገው እርዳታ በተጨማሪ እርዳታውን ለተጎጂዎች እንዴት ማድረስ ይቻላል የሚለውም አሳሳቢ ጉዳይ ነው ።

https://p.dw.com/p/2c1yd
UN Geberkonferenz Jemen in Genf Guterres und Wallstrom
ምስል picture-alliance/dpa/V. Flauraud

Q&A Yemen crisis &Donors conference in Geneva - MP3-Stereo

የርስ በርስ ጦርነት በሚካሄድባት በየመን በገባው ረሀብ ለተጎዱት መርጃ የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ  ከትናንት በስተያ ጄኔቫ ስዊትዘርላንድ በተካሄደው የለጋሽ ሀገራት ጉባኤ ላይ ከሚያስፈልገው ገንዘብ ግማሽ ያህል ቃል ተገብቷል ። ጉባኤውን የመሩት የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶንዮ ጉተሬስ  ድርጅቱ በዚህ ዓመት ለየመን ያስፈልጋል ያለውን ገንዘብ በሙሉ የሚያገኝ ባይሆንም ግማሹንም ቢሆን ለመስጠት ቃል የገቡትን አወድሰዋል ። በአሁኑ ጊዜ በየመን በረሀብ ለተጎዱት ከሚያስፈልገው እርዳታ በተጨማሪ እርዳታውን ለተጎጂዎች እንዴት ማድረስ ይቻላል የሚለውም አሳሳቢ ጉዳይ ነው ።ስለ እርዳታ አሰባሰቡ እና በየመን ለበረሀብ ለተጎዱት እርዳታ ለማድረሱ በሚያጋጥመው ችግር ላይ የብራሰልሱን ወኪላችንን ገበያው ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።