የዚምባቡዌ ፖለቲከኞች ሽኩቻ
ዓርብ፣ ጥቅምት 21 2007ማስታወቂያ
የዚምባቡዌ ተጣማሪ መንግሥት መስራች ፓርቲዎች አንዳቸዉ ከሌላቸዉ ጋር የሚደርጉት ሽኩቻ አልበቃ ያለ ይመስል በየዉሳጣቸዉም ለሥልጣን መፋተጋቸዉ እየተነገረ ነዉ።ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ዚምባቡዌን ለረጅም ጊዜ የገዛዉ የዛኑ-ፒ ኤፍ ፖለቲከኞች አንጋፋዉን የነፃነት አርበኛ እና መሪ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤን ለመተካት እርስ በርስ እየተጠላለፉ ናቸዉ።ከዛኑ-ፒ ኤፍ ጋር ተጣማሪ መንግሥት የመሠረተዉ የዴሞክራሲያዉዊ ለዉጥ ንቅናቄ (MDC) አንዳድ ፖለቲከኞችም የፓርቲዉ መሪ ሞርጋን ሻንግራይ ሥልጣን ያስረክቡ የሚል ጥያቄ አንስተዋል።የዶቸ ቬለዉ ማርክ ካልድዌል ሻንግራይን አነጋግሯቸዋል።ይልማ ሐይለ ሚካኤል እንደሚከተለዉ አጠናቅሮታል።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ