የዓርብ ዕለቱ የቦምብ ፍንዳታ በአንዋር መስጊድ
ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 2 2008ማስታወቂያ
አቶ ጌታቸው ረዳ «እስካሁን ጥቃቱን ማን እንደፈጸመው የምናውቀው ነገር የለም።» ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል። በመርካቶ በሚገኘው ታላቁ አንዋር መስጊድ የደረሰው የቦምብ ፍንዳታው ከዓርብ የጁምዓ ጸሎት በኋላ ነበር። ለመንግስት ቅርበት ያለው ሬዲዮ ፋና በበኩሉ በፍንዳታው የተጎዱ ሰዎች ቁጥር 24 መሆኑን ዘግቧል። በፍንዳታው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በቅዱስ ጳውሎስና ተክለሃይማኖት ሆስፒታሎች ህክምና እንደተደረገላቸው ዘግቧል። እስካሁን ለፍንዳታው ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም። በአደጋው በአምስት ሰዎች ላይ ከባድ በ19 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የመቁሰል አደጋ መድረሱን የዘገበው የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቭዥን የፍንዳታው መንስዔ «ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ የተወረወረ ቦምብ» መሆኑን የፌደራል የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል መግለጫን በመጥቀስ ዘግቧል።
እሸቴ በቀለ
ልደት አበበ