የዓለም የስነህዝብ ቀንና ኢትጵያ
ረቡዕ፣ ሐምሌ 4 2004ማስታወቂያ
በዓለም 220 ሚሊዮን የሚሆኑ ሴቶች ወሊድ መከላከያ እየፈለጉ ማግኘት እንደማይችሉ የተመድ አስታወቀ። ዛሬ የዓለም የስነህዝብ ቀን ሲታሰብ ሎንዶን ላይ የተካሄደዉ ጉባኤ በአዳጊ ሀገሮች ዉስጥ ለሚኖሩ 120 ሚሊዮን ሴቶች የወሊድ መቆጣጠሪያ ስልቶችን በተገቢዉ መጠን ለማዳረስ ወደ4 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ አልሟል። ዕለቱን አስመልክቶ ኢትዮጵያ የተካሄደ አንድ አዉደ ጥናት ደግሞ ሀገሪቱ በፍጥበት እያደገ የሚሄደዉን የህዝቧን ቁጥር ማመጣጠን ካልቻለች ከድህነት አዙሪት ለመዉጣት የጀመረችዉን ጥረት ያለፍሬ ሊያስቀረዉ እንደሚችል ማመልከቱን ወኪላችን ታደሰ እንዳዉ የላከዉ ዘገባ ያስረዳል። ኢትዮጵያ የህዝቧን ቁጥር እድገት ለመመጠን ከፍተኛ ቁጥጥር ያለዉ መርህ መከተል እንደሚገባትም ተገልጿል።
ታደሰ እግዳዉ
ሸዋዬ ለገሠ