የዓለም ዋንጫው ማጣሪያና ኢትዮጵያ
ሰኞ፣ ሰኔ 10 2005ማስታወቂያ
ይሁንና የዓለም እግር ኳስ ፌደሬሺኖች ማሕበር ፊፋ ቡድኑ ከሣምንት በፊት ቦትሱዋና ውስጥ ባደረገው ግጥሚያ አንድ ያልተፈቀደለት ተጫዋቹን ሳያሰልፍ አልቀረም ሲል ዛሬ በከፈተው ምርመራ መልሶ ሶሥት ነጥቦች እንዳያጣ እያሰጋው ነው። እርግጥ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተሸናፊ ተደርጎ ቢፈረድበትም ምድቡን በሁለት ነጥቦች ልዩነት መምራቱን የሚቀጥል ሲሆን ከማዕከላዊት አፍሪቃ ሬፑብሊክ ጋር በሚያካሂደው የምድብ-አንድ መጨረሻ ግጥሚያ አሸንፎ ወደ ተከታዩ ዙር የማለፍ ትልቅ ዕድል አለው። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መቀጣት ደቡብ አፍሪቃን እንደገና ከሞት የሚመልስ ነው የሚሆነው። በጉዳዩ ዛሬ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ቡድን ዋና አሠልጣኝ አቶ ሰውነት ቢሻውን በስልክ አነጋግረናል፤ ያድምጡ!
መሥፍን መኮንን
አርያም ተክሌ