1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም አቀፉ የወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤትና አፍሪቃ

ሰኞ፣ ኅዳር 13 2008

የዓለም አቀፍ ወንጀል ፍርድ ቤት፤ ፍርድ ቤቱ የተቋቋመበትንና ሰነድ የተቀበሉትንና የፈረሙትን አባል ሀገሮች የሚያካትተዉን ዓመታዊ ጉባኤ ካለፈዉ ሳምንት ረቡዕ ጀምሮ እስከ ያዝነዉ ሳምንት ረቡዕ ድረስ ዘ ሄግ ኔዘርላንድስ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

https://p.dw.com/p/1HAv6
GMF Logo Interantional Crime Court ICC

የዓለም አቀፍ ወንጀል ፍርድ ቤት፤ የፍርድ ቤቱን ደንብ ሥልጣንና ኃላፊነት የሚደነግገዉን የሮማ ሰነድ የተባለዉን የፍርድ ቤቱን መመስረቻ ሰነድ በተቀበሉ አባል አገሮች እንደ ጎርጎርዮሳዊዉ አቆጣጠር 2002 ዓ,ም የተቋቋመና ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን እንዲዳኝ ስልጣን የተሰጠዉ የፍትህ ተቋም ነዉ። የፍርድ ቤቱ መሰረታዉ ሰነድ የሆነዉ የሮማዉ ሰነድ በዓለም ዙርያ በሰባዊነት ላይ የተፈፀሙና እየተፈፀሙ ያሉ ወንጀሎችን የዘር ማጥፋትንና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን በዓለም አቀፍ ወንጀለኝነት በመፍረድ እነዚን ወንጀሎች መንግሥታት በራሳቸዉ መመርመርና መዳኘት ካልቻሉ ወይም ካፈለጉ ፍርድ ቤቱ እንዲያጣራና ካልቻሉ ወይም ካልፈለጉ ፍርድ ቤቱ እንዲያጣራና እንዲያስችል ስልጣን ይሰጣል።

Omar Hassan Ahmad al-Bashir Präsident Sudan Internationalen Strafgerichtshof Logo
ምስል picture-alliance/dpa/Montage DW

የዚህን ፍርድ ቤት ስልጣንና ኃላፊነት የሚደነግገዉን የሮማን ሰነድ የተቀበሉትም አገሮች የፍርድ ቤቱን የሚያስተዳድሩ ሲሆን፤ በየዓመቱ በሚያደርጉት ጉባዔም የፍርድ ቤቱን የሥራ ሂደት ይመረምራሉ፤ መመርያም ይሰጣሉ። ዘንድሮ ግን ጉባኤዉ ፍርድ ቤቱንና የአፍሪቃ መንግሥታት የተወዛገቡበትና እሰጣ ገባ የበዛበት እንደሆነ ነዉ፤ ከጉባኤዉ የወጡት ምንጮች የሚያስረዱት ። የዛሬው ዜና ማህደር፣ የዓለማቀፉን የወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤትና የአፍሪቃ መንግሥታትን ዉዝግብ ፤ እንዲሁም የፍርድ ቤቱን እጣ ፈንታ በሚመለከት የባለሞያን አስተያየትን አካቶ የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ያስቃኘናል።

ገበያዉ ንጉሴ


አርያም ተክሌ