የወጣቶች ዓለም
ዓርብ፣ ሰኔ 8 2004ማስታወቂያ
በርካታ ወጣቶች በመዝናኛ ዕጦትም ይሆን በሌሎች ምክንያቶች አብዛኛውን የትርፍ ጊዜያቸውን በአልባሌ ቦታዎች ሲያሳልፉ መመልከት የተለመደ ሆኗል። በዛሬው የወጣቶች መድረክ ዝግጅታችን ያነጋገርናቸው ወጣቶች ግን በተለያዩ የስነፅሁፍ ክበባት ውስጥ በመንቀሳቀስ ራሳቸውን ከጎጂ ድርጊቶች በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ፤ ስለእንቅስቃሴያቸው ይገልፁልናል።
ናዝሬት ከተማ ውስጥ የተለያዩ ወጣቶች በኪነጥበቡ እና ማኅበራዊ አገልግሎት በመስጠቱ ዘርፍ ተሰማርተው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉት ወጣቶች ደግሞ ጫት መቃምን በመሳሰሉ ጎጂ ልማዶች ተጠምደው እንደሚገኙ በተደጋጋሚ ይጠቀሳል።
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ