1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኬንያ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ ያሳለፈው ብይን

ሰኞ፣ መስከረም 17 2003

ስደተኞቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የበየነባቸው ፍርድ ቤት የገንዘብ ቅጣትም ጥሎባቸዋል

https://p.dw.com/p/PNuX
ምስል picture-alliance / dpa

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከሚንገላቱባቸው አገራት አንዷ ኬንያ ናት ። በኬንያ የተለያዩ አካባቢዎች የስደት ኑሮ የሚገፉ ኢትዮጵያውያን በልዩ ልዩ ምክንያቶች ለእስር እና ለወከባ እንደሚዳረጉ በየጊዜው የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ ። በቅርቡ ደግሞ ሰማንያ ዘጠኝ የሚሆኑ ኬንያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲባረሩ በፍርድቤት ተወስኖባቸዋል ። ። በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ስለተላለፈው ስለዚሁ ብይን መሳይ መኮንን አንድ ኬንያዊ ጋዜጠኛ እና አንድ ኬንያ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ስደተኛ አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል ።

መሳይ መኮንን

አርያም ተክሌ