1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኬንያ ዘመቻ በሶማሊያ

ሰኞ፣ ሰኔ 25 2004

በሰሜን ኬንያ በሁለት ዓብያተ-ክርስቲያን ላይ በደረሰ የቦምብ ጥቃት ቢያንስ 17 ሰዎች ሲገደሉ አርባ የሚሆኑም ቆስለዋል። ጥቃት አድራሾቹ ጥቃት ከጣሉ በኋላ ማንነታቸው ሳይታወቅ ሸሽተው ተሰውረዋል።

https://p.dw.com/p/15Q0u
Somalia. REUTERS/Stringer (KENYA - Tags: SOCIETY CIVIL UNREST CRIME LAW RELIGION)
ሰኔ 24 2004 ዓ ም በኬንያ ቤተ ክርስትያንምስል Reuters

ለጥቃቱ እስካሁን ኃላፊነት የወሰደ ቡድን ባይኖርም ኬንያ የምትጠረጥረው አሸባብን ነው።

ትናንት በኬንያ ጋሪሣ ከተማ በተጣለው ፈንጅ ቢያንስ 17 ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል። እንደዚህ አይነቱ በዓብያተ-ክርስቲያን ላይ የተጣለ ጥቃት ምን ያመላክታል? በአለም አቀፍ የፀጥታ ጥናት ተቋም- ISS የሶማሊያ ተንታኝ -ኢማኑኤል ኪሳንጋኒ

Members of the Kenyan security forces keep onlookers back from the scene outside the African Inland Church in Garissa, Kenya Sunday, July 1, 2012. Gunmen killed two policemen guarding a church, snatched their rifles and then opened fire on the congregation with bullets and grenades on Sunday, killing at least 10 people and wounding at least 40, security officials said, with militants from Somalia being immediately suspected. (AP Photo/Chris Mann)
በደረሰው አደጋ ቢያንስ 17 ሰዎች ተገድለዋለ። 40 የሚሆኑ ቆስለዋል።ምስል AP

« ቀደም ሲል በውጭ አገር ዜጎች ላይ ነበር ጥቃት የሚጣለው። ነገር ግን ኬንያ ጣልቃ ከገባች በኋላ ተራ ኬኒያውያን ኢላማ የሚሆኑበት አዲስ የጥቃት አቅጣጫ ይታያል። ። እና ጥቃቱ በዓብያተ ክርስትያን ላይ መጣሉ የሚያመላክተው የአሸባብ ደጋፊዎች ወይንም አሸባብ ራሱ በሶማሊያ ያለውን ግጭት ልክ በክርስትያን እና ሙስሊሞች መካከል እንዳለ ግጭት አድርጎ ለማጠቃለል መሞከሩን ያመላክታል። እንደሚመስለኝ የትናንትነው ጥቃት ለዚህ ማረጋገጫ ይሆናል።»

ኪሳንጋኒ እንዳሉት ሁሉ በርካታ ተንታኞችም ኬንያ ጦሯን ወደ ሶማሊያ ካዘመተች በኋላ አሸባብ ጥቃት ሊጥልባት እንደሚችል አስጠንቅቀው ነበር። ለሶማሊያ ድንበር ቅርብ በሆነችው የኬንያ ጋሪሣ ከተማ እንዲሁም በዳዳብ የስደተኞች መጠለያ አካባቢ በተደጋጋሚ አሸባብ ከዚህ ቀደም ጥቃቶች አድርሷል።

« በነዚህ በተወሰኑ አካባቢዎች በተደጋጋሚ የቦምብ ጥቃት ከዚህ ቀደም ሲጣል ነበር። ያሁኑ ግን ከሁሉም ትልቁ ነው። የኬንያ በግልፅ ጣልቃ መግባት ጥቃቱ እንዲደርስ አድርጓል። ስለዚህ አስገራሚ አይደለም። ይሁንና ሰዎች እንደዚህ ቁጥሩ ከፍ ያለ 17 አሁን ደግሞ 18 ሰዎች የሞቱበት ጥቃት በዓብታተ ክርስትያን ላይ ይጣላል ብለው አልጠበቁም።»

Pro-Palästina Demonstration der Al-Shabaab Miliz in Somalia
የአሸባብ ወታደሮችምስል picture-alliance/Photoshot

ኬንያ ባለፈው ጥቅምት ወር አክራሪውን የዓማፂ ቡድን አሸባብን ለመውጋት ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ ካሻገረች ወዲህ በተደጋጋሚ የጥቃት ዒላማ ሆና ቆይታለች። በኃገሪቷ ጠንካራ የሆነ የደህንነት ጥበቃ የለምን? ኪሳንጋኒ?

« ሰዎች የወንጀል መርማሪው ክፍል የብሔራዊ ፀጥታ መ/ቤት የት ናቸው? ምን እየሰሩ ነው? እንዴት እንደዚህ አይነቱን ነገር ሊከላከሉ አልቻሉም ይላሉ። ሆኖም ሁላችንም እንደምናውቀው አንዳንዴ የሽብር ጥቃቶችን መከላከል ከባድ ነው። አስቀድመው ስለ ጥቃቱ አይናገሩም። በተጨማሪ የእያንዳንዱን ዜጋ ደህንነት በተናጠል ማስጠበቅ አዳጋች ነው። ምክንያቱም ብዙ የፖሊስ ወታደሮች አስፈላጊ ናቸውና። በዮናይትድ እስቴትስ የመስከረም አንዱን ጥቃት ተመልክተናል። ያ ሁሉ ቴክኖሎጂ ያላት አሜሪካም ተጠቅታለች።»

Kenyan security forces secure the scene of an attack at the African Inland Church in Kenya's northern town of Garissa July 1, 2012. Masked attackers killed at least 17 people on Sunday in gun and grenade attacks on churches in a Kenyan town used as a base for operations against al Qaeda-linked insurgents in Somalia. REUTERS/Chris Mann (KENYA - Tags: RELIGION CIVIL UNREST)
በኬንያ ዓብያተ ክርስትያን ላይ የደረሰው ጥቃትምስል Reuters

ስለሆነም ይላሉ ኪሳንጋኒ ኬኒያውያን መንግስት ለደህንነት የበለጠ ትኩረት ይስጥ የሚሉት አግባብ ነው ይሁንና እንደዚህ አይነቱን ጥቃቶች ሙሉ ለሙሉ ለማስቆም ከባድ ነው።

አሸባብን ለመዋጋት የጦር ኃይሏን የላከችው ኬንያ ብቻ አይደለችም። እንደ ኢትዮጵያ እና ዮጋንዳ የመሳሰሉ አገሮች ጦራቸውን ወደ ሶማሊያ ልከዋል። በተደጋጋሚ ግን ጥቃት ሲጣል የሚታየው በኬንያ ላይ ነው ለምን? ኪሳንጋኒ መልስ ሰተውናል።

«ቁጥራቸው ከፍ ያለ ኢትዮጵያውያን ለረዥም ጊዜ ሶማሊያ ውስጥ ነበሩ። የኢትዮጵያ ወታደሮች ከ2006 ዓ ም አንስቶ ወደ ሶማሊያ የእስላማዊ ኃይል ህብረትን ለመዋጋት ዘምተዋል። በጊዜ ብዛት ሊደርስ ከሚችል ማንኛውም ጥቃት ራሳቸውን መጠበቅ ችለዋል። ዮጋንዳ ላይ በ2010ሩ የአለም ዋንጫ ጊዜ አደጋ ተጥሎ ነበር።»

ልደት አበበ

ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ