1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦሮምያ ክልል ዕቅድና ትችቱ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 7 2008

ዕቅዱ የተለጠጠ እና ለፖለቲካ ፍጆታ የታሰበ ነው የሚሉ ትችቶች እየተሰነዘሩበት ነው።

https://p.dw.com/p/1IWgh
Fegadu Tesema Sprecher Oromo Bevölkerung Demokratische Partei
ምስል DW/Y. G/Egziabhare

[No title]

የኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከ832 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ እድል ለመፍጠር ያወጣው እቅድ እያነጋገረ ነው። የክልሉ መንግሥት እንደሚለው እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ 2.4 ቢሊዮን ብር ተመድቧል። የመጀመሪያውን ዙር ሥራ በተግባር ለመተርጎም 300 ሚሊዮን ብር ተመድቦ እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ለዶቼቬለ አስታውቋል። ኃላፊው እንዳሉት የዕቅዱ ይዘትና አተገባበር ላያ ያተኮረ ሥልጠናም ለወጣቱ እየተሰጠ ነው። ዕቅዱ የተለጠጠ እና ለፖለቲካ ፍጆታ የታሰበ ነው የሚሉ ትችቶች እየተሰነዘሩበት ነው። የአዲስ አበባዉ ዘጋቢያችን ዝርዝር ዘገባ አዘጋጅቷል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ