የእድገትና ለዉጥ እቅድ
እሑድ፣ መጋቢት 15 2005ማስታወቂያ
ከ 80 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላትን፤ በዓለም ውስጥ እጅግ ከደኸዩት አገሮች አንዷ ፣ በመሠረታዊ ልማትም፣ ገና ብዙ የቀራትን ሀገር ፣ በ 5 ዓመት ውስጥ አንድ ከፍ ያለ እመርታ እንድታደርግ ፤ ውጤት ማስገኘት የሚቻልባቸውን ቅድመ ግዴታዎች መርምሮና ግምት ውስጥ አስግብቶ ለመንቀሳቀስ ማሰብ ፣ ማቀድ በራሱ አዎንታዊ ነው።
ከ 2002 እስከ 2007 የሚዘልቀው፣ በዋናነት ግብርናና ኢንዱስትሪ ተኮር መሆኑ የሚነገርለት የኢትዮጵያው አጠቃላይ የዕድገትና ለውጥ አቅድ ከ 75-79 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስወጣ ነው የተገመተው። የዕድገትና የለውጥ(ትራንስፎርሜሽን) እቅዱ ፣ የግማሽ ዘመን(የ 2 ዓመት ከመንፈቅ )ሂደትና ውጤት ፣ ከወዲያኛው ሰሞን የተገመገመበት የጥናት ውጤት ሲቀርብ፤ ፣ መንግሥት ፣ ምንም እንኳ የኤኮኖሚው ዕድገት እንደታቀደው 11 ከመቶ ሳይሆን በ 8,5 ከመቶ የተወሰነ ሆኖ ቢገኝም፣ ኤኮኖሚው ጠንካራ ነው ሲል መግለጹ የሚታወስ ነው። ሙሉ ዉይይቱን ያድምጡ።
ተክሌ የኋላ
ልደት አበበ