1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእናት ጓዳ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 13 2000

እዚህ በምዕራቡ አለም ቀመም ያልበዛበት መዐዛዉ ጠንከር ያላለ ምግብ የሚበላ የነበረዉ ህዝብ ለመጀመርያ ግዜ የህንድ እና የቻይናዉያን ምግብ ቤት ከፍተዉ ባህላቸዉን ሲያስተዋዉቁ የምግቡ መአዛ የረበሸዉ ክስ የቀረበ ነበር አሉ

https://p.dw.com/p/E0li
ምስል picture-alliance/dpa

እንዲህ እንዳሁኑ ዘመን ተቀይሮ በየ10 ሜትሩ በቅመም ያበደዉ የህንድ እና የቻይና ምግብ አዳራሽ ተወዳጅ ሳይሆን፣ ከሰማንያ በላይ ብሄር ብሄረሰቦችን የያዘችዉ የኢትዮጻያ የተለያዩ ጣዕም ያላቸዉ ባህላዊ ምግቦችም በአዉሮጻዉያን ዘንድ ተወዳጅነታቸዉ ታዋቂነታቸዉ በመጉላት ላይ ይገኛል፣ የዛሪዉ የባህል መድረካችን በለንደን ሆርን አፍሪካ ፉድ በተሰኘ የኢትዮጽያን ምግብ ከሚያስተዋዉቁ ባለሞያ ወይዘሮ ጋር ያስተዋዉቀናል መልካም ቆይታ።