1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእነ ሃብታሙ አያሌው የፍርድ ቤት ውሎ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 3 2008

የተቃዋሚዎቹን የአንድነት የሰማያዊ እና የአረና ትግራይ ፓርቲ አባላት ጉዳይ የተመለከተው ፍርድ ቤት በነፃ እንዲሰናበቱ ቢወሰንላቸውም አቃቤ ህግ ውሳኔው እንዲታደግ ያቀረበውን አቤቱታ ነበር የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ያዳመጠው ።

https://p.dw.com/p/1GoTY
Waage der Göttin Justitia
ምስል picture-alliance/dpa

[No title]

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ሃብታሙ አያሌው መዝገብ አቃቤ ህግ ያቀረበውን ይግባኝ ዛሬ አዳመጠ። ፓርቲያቸውን ሽፋን በማድረግ ህገ መንግሥታዊ ስርዓቱን ለመናድ በማሴር የተከሰሱትን ከአንድ ዓመት ከሁለት ወር በፊት የታሰሩትን 4 የአንድነት የሰማያዊ እና የአረና ትግራይ ፓርቲ አባላት ጉዳይ ከዚህ ቀደም የተመለከተው ፍርድ ቤት በነፃ እንዲሰናበቱ ቢወሰንላቸውም አቃቤ ህግ ውሳኔው እንዲታደግ ያቀረበውን አቤቱታ ነበር የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ያዳመጠው ።ችሎቱ በ4ቱ ፖለቲከኞች ጉዳይ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ