የእስራኤል ዉሳኔና አፍሪቃ ሥደተኞች
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 25 2004ማስታወቂያ
የእስራኤል መንግሥት አፍሪቃዉያን ስደተኞች ወደ ሐገሩ እንዳይገቡ ለማገድ ሐገሩን ከግብፅ ጋር የሚያዋስነዉን ድበር ሙሉ በሙሉ በግንብ ለማሳጠር ወሰነ።የእስራኤል ካቢኔ ባለፈዉ እሁድ ባሳለፈዉ ዉሳኔ መሠረት ከዚሕ ቀደም የተጀመረዉን ግንብ ለማጠናቀቅና የስደተኞች ማቆያ ጣቢያ ለማሠራት አንድ መቶ ስልሳ ሚሊዮን ዶላር ተመድቧል።ካቢኔዉ ከዚሕም በተጨማሪ እስካሁን እስራኤል የገቡ አፍሪቃዉያን ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ቆይተዉ ወደየሐገራቸዉ እንዲመለሱ ወስኗል።እርምጃዉን የስደተኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተቃዉመዉታል።ሥለ ጉዳዩ የሐይፋዉ ወኪላችን ግርማዉ አሻግሬን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ግርማዉ አሻግሬ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ