የኤቦላ የኤኮኖሚ ተፅእኖ በምዕራብ አፍሪቃ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 1 2006ማስታወቂያ
የኤቦላ ወረርሽኝ በርካታ ሰዎችን የገደለበትን ምዕራብ አፍሪቃን ከሁለት አቅጣጫ አደጋ ላይ ጥሏል ። በአካባቢው እስካሁን በሽታው የገደላቸው ሰዎች ቁጥር ከዕለት ወደ እለት እየጨመረ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ከመድረሱም በላይ በሽታው ያስከተለው የኤኮኖሚ ቀውስም ቀላል የሚባል አይደለም ።በንክኪና ከሰውነት በሚወጣ ፈሳሽ በሚተላለፈው በገዳዩ ኤቦላ ምክንያት ተውሃሲው በተሰራጨባቸው ሃገራት የንግድ ልውውጥ ቀንሷል ።የአገልግሎት ሰጭ የንግድ ተቋማት ገበያም ቀዝቅዟል ። የተለያዩ አየር መንገዶች ወደ ምዕራብ አፍሪቃ የሚያካሂዷቸውን በረራዎች ማቆማቸው የሃገራቱን ኤኮኖሚ እየጎዳ ነው ።
ፊሊፕ ዛንድነር
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ