1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤርትራውያን የተቃውሞ ሰልፍ በሮም

ዓርብ፣ ጥቅምት 15 2006

በኢጣሊያ የሚኖሩ ኤርትራውያን ባለፈው ወር በጀልባ አደጋ ያለቁ ዜጎችን ለማሰብ ዛሬ በሮም አደባባይ ወተዋል።

https://p.dw.com/p/1A6OV
Titel: Flüchtlinge am Brandenburger Tor Schlagworte:Flüchtlinge, Brandenburger Tor, Hungerstreik, Berlin, Lampedusa Wer hat das Bild gemacht?: DW/Lavinia Pitu Wann wurde das Bild gemacht?: 14.10.2013 Wo wurde das Bild aufgenommen?: Berlin, Pariser Platz Bildbeschreibung: Flüchtlinge befinden sich seit mehreren Tagen im Hungerstreik, am Pariser Platz. Sie verlangen Asyl in Deutschland und Änderungen der deutschen Einwanderungspolitik.
ምስል DW/L. Pitu

ጀርመንን ጨምሮ ከተለያዩ የኣውሮፓ ኣገሮች የመጡ ኤርትራውያንም በሰልፉ ላይ የተገኙ ሲሆን የሰልፉ ዓላማ የኣውሮፓ ህብረት ስደተኞችን ኣስመልክቶ ያለውን ኣሳሪ ህግ እንዲያሻሽል ለመጠቀቅ ነው ተብለዋል።

ሰልፈኞቹ የዚህ ሁሉ መከራ ዋናው መንስዔ ነው ያሉትን የኤርትራን መንግስትም ያወገዙ ሲሆን የኢሳያስ አፈወርቂን ፎቶግራፍ በአደባባይ ሲቀዱም ተስተውለዋል።

በርካታ ኤርትራውያን የተለያዩ መፈክሮችን ይዘው ሞንቴቺቴሪዮ በሚባለው እና ከጣሊያን ፓርላማ ፊትለፊት ወደሚገኘው ታሪካዊ አደባባይ የተመሙት ዛሬ ከረፋዱ ጀምሮ ነበር። የሰልፉ ዓላማ ባለፈው ወር በላምፔንዱዚው የጀልባ አደጋ ያለቁትን ኤርትራውያን ለማሰብ ሲሆን ካነገቡኣቸው መፈክሮች መካከልም በርካቶቹ እነዚህኑ ሰማዕታት የሚያስታውሱ ነበሩ።

ሰልፈኞቹ ሞንቴቺቴሪዮ አደባባይ እንደ ደረሱም በኦርቶዶክስ በካቶሊክ እና በእስልምና ኃይማኖት አባቶች እየተመሩ ሙታኑን በጸሎት ኣስበዋል።እንደየ ኃይማኖቱ ወግ መሰረትም ስርዓተ ፍትኃት ተደርጎላቸዋል። በተለይም በሰልፈኞቹ የተዘጋኙት የሬሳ ሳጥኖች በቀሳውስቱ እየተመሩ እና በኣሳዛኝ ኤርትራዊ ዜማ ታጅበው ኣደባባዩን ሲዞሩ የዶቸቬሌው ዘጋቢ ተክለግዚ ገ/እግዚኣብሔር ከስፍራው እንደዘገበው በእንባ ያልተራጨ ሰልፈኛ ኣልነበረም።

A Tunisian would-be immigrant walks past the Italian navy ship San Marco in the harbour of the Italian island of Lampedusa on March 30, 2011. Tension is rising on the Italian Mediterranean island of Lampedusa over the thousands of immigrants arriving from Libya, with patience running out as the numbers grow. More than 2,000 people have fled Libya by boat to Malta and Italy, but none among them appear to be Libyans according to a spokeswoman from the UN High Commissioner for Refugees (UNHCR). AFP PHOTO / ALBERTO PIZZOLI (Photo credit should read ALBERTO PIZZOLI/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images

ለቅሶ ይብቃ ከሚለው መፈክር በተጨማሪም ኤርትራ ክፍት ወህኒ ቤት ናት አንባገነንነት ይብቃ የኢሳያስ አፈወርቂ ኣንባገነናዊ ኣገዛዝ ይወገድ የሚሉ እና ሌሎችም መፈክሮች ተስተጋብተዋል። በትልቁ ተስሎ በቀይ X የተደረገበት የኢሳያስ አፈወርቂ ፎቶም ሲወገዝ እና ሲቀደድ ተስተውለዋል።

GettyImages 185481655 AGRIGENTO, ITALY - OCTOBER 21: A banner with the message 'the presence of the Eritrean regime offends the victims and endangers the survivors' is diplayed during the commemoration ceremony for the victims of the boat sinking disaster off the Lampedusa coast on October 21, 2013 in San Leone near Agrigento, Italy. Victims of the Lampedusa disaster, which killed more than 300 asylum seekers when the boat they were on sank have been buried in unknown vaults despite Italian Prime Minister Enrico Letta's promise to hold a state funeral for the dead. (Photo by Tullio M. Puglia/Getty Images)
ምስል Tullio M. Puglia/Getty Images

የዚህ ሰልፍ ዋናው ዓላማ በኢጣሊያ የዲሞክራሲያዊት ኤርትራ ሰልፍ ኣስተባባሪ አቶ ደስበለ መኃሪ እንደሚሉት በኣሰቃቂ ሁኔታ የሞቱትን ወገኖች ማሰብ ብቻም ኣልነበረም።የኢጣሊያ መንግስትም ሆነ የኣውሮፓ ህብረት ስለ ስደተኞች ያላቸውን ኣመለካከት እንደገና እንዲመረምሩ ለመጠየቅ እና ኣንባገነናዊውን የኣስመራ መንግስትም ለማውገዝ ጭምር እንጂ።

በሰልፉ ላይ ከኢጣሊያ ብቻም ሳይሆን ጀርመን እና ፈረንሳይን ጨምሮ ስዊድን እና ኖርዌይም ሳይቀሩ ከኔዘርላንድ እና ከሌሎችም የኣውሮፓ ኣገሮች የመጡ ከ500 በላይ ኤርትራውያን ተገኝተዋል። በሰልፉ ላይ ለመገኘት ከጀርመን የመጡት ዶ/ር ሳህለ ተስፋዬም ለተለያዩ ኣገሮች የሚሰራጭ ያሉትን ፔቲሺን ለጣሊያን መንግስት ለማስጠት ይዘው መምጣታቸውን ለዶቸቬሌ ነግረዋል።

በጉዳዩ ላይ ሮም የሚገኘውን የኤርትራ ኢምባሲ ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ግን ኣልተሳካም።

ባለፈው ወር በደረሰው የላምፔንዱዚው የጀልባ አደጋ በአብዛኛው ምናልባትም ከሞላ ጎደል ኤርትራዊያን የሆኑ 366 ስደተኞች ህይወታቸውን ማጣታቸው የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ 157 ያህል ደግሞ መትረፋቸው ኣይዘነጋም።

ጃፈር ዓሊ

ሂሩት መለሰ