1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤርትራዉያን ተቃዉሞ በዋሽንግተን ዲሲ

ዓርብ፣ የካቲት 1 2005

በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢዋ የሚገኙ ኤርትራዉያን እና የኤርትራ የፖለቲካ ተቋማት እንዲሁም የሲቪክ ማኅበራት በጋራ የጠሩት የተቃዉሞ ሠልፍ በኤርትራ ኤምባሲ ደጃፍ ዛሬ የካቲት 1 ቀን 2005ዓ,ም በሀገሩ አቆጣጠር ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ከዋሽንግተን የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።

https://p.dw.com/p/17bCY
ምስል AP Graphics

ይኸዉ የተቃዉሞ ሰልፍ የተጠራዉ በቅርቡ አስመራ ዉስጥ የተደረገዉን የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተቃዉሞ በመደገፍ መሆኑን ስምረት ኤርትራዉያን የተሰኘዉ የተቃዉሞ ሰልፉ አስተባባሪ ገልፀዋል። በዚሁ ሰልፍ ላይ የኤርትራ መንግስት ህገመንግስት እንዲፀድቅ፤ የተቃዋሚ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱና ሰብዓዊ መብት እንዲከበር የሚሉና ሌሎች አስር ነጥብ የያዙ ጥያቄዎች ለኤርትራ ኤምባሲ እንደሚቀርቡ የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል አመልክተዋል።

አበበ ፈለቀ

ሸዋዬ ለገሠ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ