የኤርትራና የካናዳ ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ
ሐሙስ፣ ግንቦት 22 2005ማስታወቂያ
የካናዳ መንግሥት በቶሮንቶ የኤርትራ ቆንስላ ጄኔራልን ካገር እንዲወጡ ማዘዙን የኤርትራ መንግሥት አላስፈላጊ ትንኮሳ በማለት አውግዞታል። የካናዳ መንግሥት ኤርትራዊዉን ዲፕሎማት ያባረረዉ ካናዳ የሚኖሩ ኤርትራዉያን ከገቢያቸዉ ሁለት በመቶዉን ለአስመራ መንግሥት ግብር ያስከፍላሉ በሚል ነበር።የኤርትራ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣዉ መገለጫዉ እንዳለዉ ግን ዲፕሎማቱ ዓለም አቀፉንም ሆነ የካናዳን ሕግ የጣሰ ምግባር አልፈፀሙም።እርምጃዉንም «ኤርትራዉያን ከመንግሥታቸዉ ማግኘት የሚገባቸዉን አገልግሎት ለመንፈግ ያለመ፥ ትንሺቱን ግን ኩሩዋን ሐገር እና ሕዝቧን ለማስፈራራት የቃጣ» በማለት አዉግዞታል። የካናዳ መንግሥት የኤርትራን የቆንስላ ጽ/ቤት ከኤርትራውያን ላይ ግብር ከመሰብሰብ እንዲታቀብ ሲያስጠነቅቅ መቆየቱ ታውቋል። አዣንስ ፍራስ ፕረስ የጠቀሰዉ የኤርትራ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ ተደጋጋሚ ማስፈራራትና በደል ይፈፀምባቸዋል ያላቸዉ በካናዳ የኤርትራ ማሕበረሰብ አባላት የሚደርስባቸዉን ችግር መቋቋም እንደሚችሉ የኤርትራ መንግሥት እርግጠኛ ነዉ ቢልም ካናዳ የሚኖሩ ኤርትራውያን በእርምጃው መደሰታቸውን አስታውቀዋል
አበበ ፈለቀ--
ተክሌ የኋላ
ሂሩት መለሰ