የኢትዮጵያ ጉዳይ በጀርመን ፖለቲከኛ እይታ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 22 2009ማስታወቂያ
ጀርመን እና የአውሮጳ ኅብረት ፣ ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ የማያደርግ ፣ ከመሬቱ የሚያፈናቅል እና በሰላማዊ ሰልፈኞችም ላይ ተኩስ ከፍቶ የሚገድል ካሉት መንግሥት ጋር መሥራት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እንደደረሱ አንድ የጀርመን ፖለቲከኛ አስታወቁ ። ይህን አሰተያየት የሰጡት ኒማ ሞቫሳት በጀርመን ምክር ቤት የግራዎቹ ፓርቲ ተወካይ ፣ ጀርመን እና የአውሮጳ ኅብረት በኢትዮጵያ ህዝብን ተጠቃሚ የማያደርጉ አሠራሮች እንዲቀየሩ ጥረት እንዲያደርጉ ለዶይቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ ጠይቀዋል። በርሳቸው አስተያየት ይህ ተግባራዊ ካልሆነ ከኢትዮጵያም ሆነ ከሌሎች የአፍሪቃ ሀገራት ወደ አውሮጳ የሚጎርፉ ስደተኞችን ማስቆም አይቻልም። የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል የጀርመን የህዝብ እንደራሴን ኒማ ሞሶቫትን አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል።