የኢትዮጵያ ጉዳይ መፅሔት በጀርመን
ሐሙስ፣ መጋቢት 6 2004ማስታወቂያ
የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚያስተዋዉቅ አዲስ መፅሔት እዚሕ ጀርመን ዉስጥ መታተም ጀምሯል።አንዲት ጀርመናዊትና አንድ ኢትዮጵያዊ በጋራ በእንግሊዘኛና በጀርመንኛ የሚያሳትሙት መፅሔት ኢትዮጵያ የረሐብና የድርቅ ሐገር ብቻ እንዳልሆነች ለአንባቢዎች ለማሳወቅ ያለመ ነዉ።አዘጋጆቹ እንዳስታወቁት መፅሔቱ በአመት አንዴ በርሊን-ጀርመን እየታተመ በሁለቱ ሐገራት ላንባብ ይሰራጫል።የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል አዘጋጆቹን አነጋግሮ የሚከተለዉን ዘገባ ልኮልናል።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ