የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ አመራር ምርጫ
እሑድ፣ መስከረም 6 2005የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ (ኢህአዴግ) ምክር ቤት በሞት የተለዩትን የግንባሩን ሊቀመንበር የሚተካ ፖለቲከኛ ለመምረጥ ለሁለት ቀናት ስብሰባ ከተቀመጠ በኋላ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን የድርጅቱ ሊቀመንበር፤ አቶ ደመቀ መኮንንን ደግሞ በም/ሊቀመንበርነት መሰየሙን ማስታወቁ የሚታወቅ ነዉ። ይህንኑ ተከትሎ የኢንፎርሜሽን እና ኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ለአገር ዉስጥ እና ለዉጭ ጋዜጠኞች መግለጫ ሰተዋል።
በመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት«መኢአድ» በኩል በኢትዮጵያ ስለ አዲሱ መራሄ መንግስት ሹመት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ መሶብወርቅ ቅጣዉ እና ተቀዳሚ ምክትል ፕሪዚደንቱ አቶ ወንድም አገኘሁ ደመቀ እንደገለጹት የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት «መኢአድ» ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅቶአል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ታዋቂ ግለሰቦች የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ደጋፊዎች የፓርቲዉ የመኢአድ አባላት እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ይገኛሉ።
ምርጫዉን ተከትሎ ከተቃዋሚዎች ጎራ ዛሪ እሁድ ስብሰባን የጠራዉ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት «መኢአድ» ከሁሉም ወገን የሚገኙ ኢትዮጵያዉያንን የሚያሳትፍ ፓለቲካዊ ዉይይት ያስፈልጋል ሲል በጉባኤዉ አፈጻጸም ቅሪታዉን ገልጾአል። ሙሉ ዝርዝሩን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሃይለ ጊዮርጊስ አዘጋጅቶታል።
ጌታቸዉ ተድላ ሃ/ጊዮርጊስ
አዜብ ታደሰ
መስፍን መኮንን