1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ የግብፅና የሱዳን ስምምነት

ማክሰኞ፣ የካቲት 15 2008

መሪዎቹ በትብብር ለመስራት የተስማሙት እዚያው ሻርም ኤል ሼክ በመካሄድ ላይ ከነበረው የአፍሪቃ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት መድረክ ጎን ለጎን ባካሄዱት ስብሰባ ነበር ።

https://p.dw.com/p/1I0eF
Äthiopien Grand Renaissance Staudamm al-Sisi al-Bashir Desalegn
ምስል Ashraf Shazly/AFP/Getty Images

[No title]

ኢትዮጵያ ግብፅና ሱዳን በሦስትዮሽ ሁለገብ የልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራት በቅርቡ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ሦስቱ ሃገራት እዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ና የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ዑመር አልበሽር ግብፅ ሻርም ኤልሼክ ውስጥ ባለፈው ቅዳሜ የጋራ ትብብራቸውን በሚያጠናክሩበት መንገድ ላይ ከተወያዩ በኋላ ነው ። መሪዎቹ በትብብር ለመስራት የተወያዩት እዚያው ሻርም ኤል ሼክ በመካሄድ ላይ ከነበረው የአፍሪቃ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት መድረክ ጎን ለጎን ባካሄዱት ስብሰባ ነበር ። ባለሥልጣናት እንዳስታወቁት በተለይ የግብፅ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ቀጣና የመገንባት እቅድ ይዘዋል ።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ