የኢትዮጵያ የመያዶች ሕግና የገጠመዉ ተቃዉሞ
ረቡዕ፣ የካቲት 25 2001ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት መንግሥታዊ ሥላልሆኑ ድርጅቶች (መያድ) ሥራና አሰራር በቅርቡ የደነገገዉ ሕግ ከተለያዩ ወገኖች የገጠመዉ ተቃዉሞ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።ትናንት በርሊን ዉስጥ በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር በተጠራ ሥብሰባ ላይ ዋና ተናጋሪ የነበሩት በጀርመን ምክር ቤት የአረንጓዴዉ ፓርቲ ተወካይ ወይዘሮ ኡተ ኮቺክ ሕጉ በሕዝብ ዘንድ ፍራቻና ጥርጣሬን የኋላ ኋላም አመፅና ሁከትን ያስከትላል ብለዉ ይፈራሉ።በጀርመን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሰደር አቶ ካሳሁን አየለ ግን ሕጉ የዉጪ ጣልቃ ገብነትን ለመቀነስ ያለመ ነዉ ባይ ናቸዉ።ይልማ ሐይለ ሚካኤል ዉይይቱን ተከታትሎታል።
Hinz,Yilma
►◄