የኢትዮጵያ ኦ.ተ.ቤ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
ረቡዕ፣ ጥር 8 2005ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የ6 ተኛው ፓትሪያርክ ምርጫ ሂደት እንደሚቀጥል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ ። ሲኖዱሱን በመወከል ብፁዕ አቡነ አብርሃም የምሥራቅ ሐረርጌ ሃገረ ስብከት ጳጳስ በንባብ ባሰሙት መግለጫ ፣ ሲኖዶሱ የቀድሞውን 4 ተኛውን ፓትሪያርክ በፓትሪያርክነት የሥልጣን ደረጃ እንደማይቀበል መወሰኑን አስታውቀዋል ። የቤተ ክርስቲያኗ ምክትል ስራ አስኪያጅ ንቡረአድ ኤልያስ አብርሃም በበኩላቸው በስደት ላይ ካለው ሲኖዶስ ጋር እርቀ ሰላም ለማውረድ መድረግ ያለበት ሁሉ መከናወኑን ተናግረዋል ። መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ