የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ስሞታና የመንግሥት መልስ
ማክሰኞ፣ የካቲት 17 2001ማስታወቂያ
ባለፈዉ ሳምንት የጋራ ሕብረት ወይም ግንባር ለመመስረት የተስማሙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎች እንደሚሉት መንግሥት መሪዎቻቸዉን፥ አባላቶቻቸዉና ደጋፊዎቻቸዉን ያላግባብ ያስራል፥ ከሥራ ያፈናቅላል፥ ነፃ መገናኛ ዘዴዎችን ያፍናል።የመገናኛ ወይም የኮሙኒኬሽን ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ አቶ አርሚያስ ለገሠ እንደሚሉት ግን የተቃዋሚዎቹ ክስና ወቀሳ በመረጃ አልተደገፈም።ታደሰ እንግዳዉ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።