1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት ስጋት

ሐሙስ፣ ግንቦት 18 2003

የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት የምርጥ ዘር ስርጭት ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ ። ድርጅቱ እንደሚለው በተለይ በቂ የተዳቀለ በቆሎ ዘር የተዘጋጀ ቢሆንም አርሶ አደሩ የሚጠበቀውን ያህል አልተጠቀመበትም ።

https://p.dw.com/p/RQCu
ምስል CC /Anne Wangalachi/ CIMMYT

ይህም በመጪው ዘመን ምርት መጠን ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ይገመታል ። የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ታፈሰ ገብሩ ለዴቼቬለ እንዳስረዱት ዘንድሮ ዝናቡ ከወትሮው በመዘግየቱና በመቆራረጡ ገበሬው ዘሩ ፍሬ ላያሰጥ ይችላል በሚል ስጋት የተዘጋጀውን ምርጥ ዘር ከመጠቀም ተቆጥቧል ። ዝርዝሩን ጌታቸው ተድላ ከአዲስ አበባ ልኮልናል ።

ሂሩት መለሰ

ጌታቸው ተድላ

ነጋሽ መሐመድ