የኢትዮጵያ ድርቅ
ዓርብ፣ ሚያዝያ 27 2009ማስታወቂያ
ዘንድሮ ኢትዮጵያን ጨምሮ ምስራቅ አፍሪቃን የመታው ድርቅ እጅግ ፈታኝ ችግሮችን ማስከተሉን የተመ የምግብ ድርጅት WFP አስታወቀ። የድርጅቱ ሃላፊ ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ WFP በተለይ በኢትዮጵያ ችግሩን ለመቋቋም የተቻለውን ሁሉ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን አስታውቀው ሆኖም ድርጅታቸው ዘንድሮ ላቀረበው የእርዳታ ጥሪ ያገኘው ገንዘብ ከሚያስፈልገው እጅግ ያነሰ መሆኑ እንዳሳሰበው ተናግረዋል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሥራ አመራር ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ተጠሪንም አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ